Friday, November 22, 2013

ኢትዮጵያ፣ በህዳርና በ… ሁልጊዜ አስታውሳለሁ!! (ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም)
     



ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
የህዳር ወር በኢትዮጵያውያን በአሰቃቂነቱ ሁልጊዜ ሲታወስ ይኖራል፡፡
እ.ኤ.አ ኖቬምበር 2013 ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በቃላት ለመግለጽ በሚዘገንን መልኩ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ ሰቆቃ የተፈጸመበት ወር ነው፡፡ ላለፉት ጥቂት ዓመታት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ፣ በሚሰሩና የፖለቲካ ጥገኝነት ለመጠየቅ ጥረት በማድረግ ላይ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ ስልታዊ የሆነ ጥቃት ሲሰነዘር ቆይቷል፡፡ እንዲያውም በግል በሚኖሩበት ቤት እምነታቸውን በማራመዳቸው ብቻ ኢትዮጵያውያኑ/ቱ ዜጎች ላይ የወንጀል ድርጊት ተፈጽሞባቸዋል፣ እንዲጋዙም ተደርጓል፡፡
እ.ኤ.አ 2011 የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ (Human Rights Watch) ዘገባ የሳውዲ አረቢያ ፖሊስ “ህገወጥ ስብሰባ በሚል ሰበብ 35 የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያወያንን/ትን“ “በአንድ ኢትዮጵያዊ የክርስትና እምነት ተከታይ የግል መኖሪያ ቤት በእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ዋዜማ ተሰባስበው ጸሎት በማድረግ ላይ እንዳሉ” በፖሊስ ቀጥጥር ስር ውለዋል” ይላል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በሳውዲ አረቢያ ጥገኝነት በሚፈልጉ እና ሌሎች ስደተኛ ኢትዮጵያውያት የቤት ሰራተኖች ላይ በሚደረገው ሰብአዊ መብት ረገጣ ምክንያት ምንጊዜም የማያቋርጥ ትችት እየተደረገ መሆኑን መግለጽ ማጋነን አይሆንም፡፡ በዚህ ወር በዕየለቱ በሚባል መልኩ የሳውዲ አረቢያ ፖሊሶች፣ የደህንነት ኃላፊዎችና ተራ የሳውዲ ዜጎች በየመንገዱ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎችን ያድናሉ፣ ይደበድባሉ፣ ያሰቃያሉ፣ አንዳንድ ጊዜም ይገድላሉ፡፡ የሳውዲ ፖሊሶች ኢትዮጵያውያንን ሲያሰቃዩ የሚያሳየው የቪዲዮ ቅርፅ ለህሊና የሚሰቀጥጥ ነው፡፡ የሳውዲዎች ኢትዮጵያውያንን በየመንገዱ የማባረር ሁከት፣ ጥቃት የመሰንዘርና የመግደል ድርጊት ምንም ዓይነት ማብራሪያ አያስፈልገውም፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ረገጣ የሚያሳየው የፎቶግራፍ ምስል አስደንጋጭና ከሰለጠነ የሰው ልጅ አስተሳሰብ በእጅጉ የዘለለ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አስተዳደር 200 ሺ እና ከዚያ በላይ የሚሆኑትን በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያን/ት ለማገዝ ምን እያደረገ ነው? ምንም!!! እራሱ አምኖ በተቀበለው መሰረት ገዥው አስተዳደር ምን ያህል ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረቢያ እንደሚኖሩ እንኩዋን አያውቅም፣ ሆኖም ግን ተጨባጭነት በሌለው መልኩ ኢትዮጵያውያንን/ትን ከሳውዲ አረቢያ ሙሉ በሙሉ በተቻለ መጠን ወደ ኢትዮጵያ እመልሳለለሁ የሚል ቃል ገብቷል፡፡
የወባ ተመራማሪው “የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር”፣ ቴዎድሮስ አድሃኖም የሳውዲ መንግስት በግዛቱ በሚገኙት ስደተኛ ኢትዮጵያውያን/ት ሰራተኞች ላይ የፈጸመውን አረመኒያዊ የኃይል እርምጃ “መንግስቱ አውግዘዋል፡፡ ይኸ በፍጹም ተቀባይነት የለውም፡፡ ይህን ጉዳዩ የሳውዲ መንግስት እንዲያጣራ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ እዚያ በነበሩበት ጊዜ በክብር መያዝ የነበረባቸውን ዜጎቻችንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስም ደስተኞች ነን፡፡ ተቀባይነት የለውም” የሚለውን አባባል ገዥው አስተዳደር እንደ አስፈሪ የጭካኔ ድርጊቶች፣ ያለመሰልጠንነትና ዘግናኝ ጨካኝነትና ወንጀለኛነት የሚሉትን ቃላት ለመግለጽ የሚጠቀምበት የውግዘት ቃል ነው፡፡ አልጄዚራ እንደዘገበው ከሆነ በተፈጸመው ድርጊት ተበሳጭተው የነበሩ ኢትዮጵያውያን/ት አዲስ አበባ በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት ሰላማዊ ተቃውሟቸውን ለማሰማት በሄዱበት ጊዜ የገዥው አስተዳደር ፖሊስ በቁጥጥር በማዋል  ድብደባ ፍጽሞባቸዋል፡፡ “ፖሊሶች ከመጡ በኋላ ደብድበውናል፣ እና በአሁኑ ጊዜ ከ100 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በእስር ቤት ይገኛሉ” በማለት የተቃዋሚው የሰማያዊ ፓርቲ ነባር አባል ጌትነት ባልቻ ገልጿል፡፡ ጌትነት በመቀጠልም “የፓርቲው ሊቀ መንበርና ምክትል ሊቀመንበር ከታሰሩት ውስጥ ይገኙበታል” በማለት ሀሳቡን አጠቃሏል፡፡
ሆኖም ግን ኢትዮጵያውያን/ በሀዳር ወር መጎዳትና መጎሳቀል ለምን ይደንቀን? እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2005 ያለው የገዢ አስተዳደር ለመናገር በሚዘገንን መልኩ የጭካኔ ድርጊት በአትዮጵያኖች ላይ ፈፅሞአል:: በዚያው ዓመት የፓርላማውን ምርጫ ተከትሎ በግንቦት ወር በጠራራ ፀሐይ የተዘረፈውን የህዝብ ድምጽ በመቀወም ድምጻቸውን ባሰሙ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች እራሱ መለስ ዜናዊ ያቋቋመው አጣሪ ኮሚሽን 193 ያልታጠቁ ወንዶች፣ ሴቶች እና ልጆች በአዲስ አበባ መንገዶች በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን በመግለጻቸውና እና ሌሎች በከፍተኛ ደህንነት በእስር ቤት የሚገኙ እስረኞችን ሆን ተብሎ በጥይት ደብድበዋል፣ ሌሎች 763 የሚሆኑት በጽኑ ቆስለዋል፡፡
እ.ኤ.አ ከ2007 ጀምሮ በየጊዜው በህዳር ወር እ.ኤ.አ የ2005 ምርጫን ተከትሎ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጨዋና ያልታጠቁ ሰልፈኞች ተኩስ በመክፈት ገደሏቸው፣ አካለ ጎደሎ አደረጓቸው፡፡ እኔም ያንን ጊዜ ለማስታወሰ ስል መጻፌን ቀጥየ ነበር፡፡
በመጀመሪያው የማሰታወስ ጽሁፌ እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2005 እና በጁን 2005 የተከፈለው መስዕዋትነት ለዘላለም ይታወሳል! ለአንባቢ ዎቼም ሳስታዉስ በህይወት ላሉትና ለሞቱት ምስክርነት መስጠት እንዳለባችሁ የሞራል ግዴታ ተጥሎባችኋል ብዬ ነበር፡፡ ኤሊ ዌይሰል የዕልቂቱ ተራፊና የኖቬል ተሸላሚ በክብር እንዳስቀመጠው “ማስታዋስ አለብን ምክንያቱም የጋራ ትውስታችን የሆኑትን ያለፉ ድርጊቶች የወደፊቱን ትውልድ መብት መከልከል ስለማንችል ነው መርሳት መጥፎ ነገር ብቻ አይደለም ነገር ግን ስድብም ነው፡፡ የሞቱትን መርሳት ሁለተኛ ከመግደል እኩል ነው፡፡”
በ2005 ያለቁትን መርሳት ማለት በእነርሱ ላይ የተፈጸሙትን ግፎች መርሳት እንዲህም ያሉትን አረመኔአዊ ወንጀል መርሳትማለት ነው፡፡ እልቂቱን መርሳት ማለት ወንጀለኞች ተጠያቂ እንዳይሆኑ የልብ ልብ መስጠት ማለት ነው፣ ምክንያቱም ወንጀሎቹ ተረስተዋል፡፡ በመጨረሻም መርሳት ማለት በስልጣን ላይ ያሉ ወንጀለኞች እንደገና እና እንደገና የወንጀል ደረጃውን ከፍ በማድረግና ተጠያቂነት የሌለበትን ሁኔታ በመፍጠር ወንጀል እንዲሰሩ ማበረታታት ማለት ነው፡፡
አስታውሳለሁ! በምንም አይነት አልረሳምም፣ በፍጹም!!!
አስታውሳለሁ ምክንያቱም እኔ ካላስታወስኩ ማን ያስታዉሳል? አስታውሳለሁ ምክንያቱም የምረሳ ከሆነ ወንጀሎችና ወንጀለኞች ይረሳሉ፡፡ የምረሳ ከሆነ ታሪክ እንዴት ሊያስታውስ ይችላል? ታሪክ ሊያስታውስ የሚችለው ሌላ ሊያስታውስ የሚችል ሰው ሲኖር ነው:: በህዳር፣ በታህሳስ፣ በጥር፣ በየካቲት፣ መጋቢት፣ ሚያዝያ… ዛሬ ለኢትዮጵያ ወጣቶችና ነገ ለሚወለዱ ህጻናት አስታውሳለሁ፡፡
የእኔን ስራ በማድነቅና ለበርካታ ዓመታት ሲደግፉ ሲቆዩ ሌሎች ደግሞ ሲተቹ ሲቃወሙ የሚኖሩ አሉ። እኔ በኢትዮጵያውያን ሰበአዊ መብቶች ችኮ ነው ይሉኛል:: በኢትዮጵያውያን ሰበአዊ መብቶች ችኮ መሆን ለኔ ታላቅ ክበር ነው::
የ2005 ዕልቂትን አስታውሳሁ፡፡ እያንዳንዱን በግፍ የተገደሉትን አስታዉሳለሁ፡፡ አስታውሳለሁ ወጣት ሴቶች ወደፊት እናት ላይሆኑ፣ ወጣት ወንዶችን የአራዊቱን  ጭፍረኞች ገዳዮችን አልረሳም  ወደፊት አባት ላይሆኑ፣ ወላጅ የሌላቸውን ወላጆቻቸው የተገደሉባቸውን አስታውሳለሁ፡፡ ልጆቻቸው የተገደሉባቸውን እናቶችንና አባቶችን አስታውሳለሁ::
ወንጀለኞችን አልረሳም፣ ተንኮል የሰሩትን 237ቱን የፖሊስ አባላት አስታውሳለሁ፣ የወንጀለኞችን ቁንጮና መሪ የነበረዉን አራዊትን  አልረሳም:: የአራዊቱን  ጭፍረኞች ገዳዮችን አልረሳም::
አስታውሳሁ፣ መቼ ረሳለሁ: ሁልጊዜ  ህዳርን፣ ታህሳስን፣ ጥርን፣ የካቲትን፣ መጋቢትን፣ ሚያዝያን…. አልረሳም፡፡
.
ስም
ጾታ
እድሜ
ስራ
 
መግለጫ
1
ሬቡማ ኢርጋታ
34
ግንበኛ
 
2
መለሳቸው አለምነው
16
ተማሪ
 
3
ሀድራ ኦስማን
22
አይታወቅም
 
 
4
ጃፋር ኢብራሂመ
28
ቢዝነስ
 
5
መኮንን
17
አይታወቅም
 
6
ወልደሰማያት
17
  
7
ባህሩ ደምለው
 
አይታወቅም
 
8
ፈቀደ ነጋሽ
25
መካኒክ
 
9
አብርሀምይልማ
17
ታከሲ ነጂ
 
10
ያሬድ እሸቴ
23
ቢዝነስ
 
11
ከበደ ገ/ህይወት
17
ተማሪ
 
12
ማቴዎስ ፍልፍሉ
14
ተማሪ
 
13
ጌትንት ወዳጆ
48
ቢዝነስ
 
14
ቃሰም ራሽድ
21
መካኒክ
 
15
ሸውሞሊ
22
ቢዝነስ
 
16
አሊየ ኢሳ
20
የቀን ስራ
 
17
ሣምሶን ያዕቆብ
23
የህዝብ ማመላ
 
18
አለባለው አበበ
18
ተማሪ
 
19
በልዩ ዛ
18
ትራንስ. ረዳት
 
20
ዩሱፍ ጀማል
23
ተማሪ
 
21
አብርሃም አገኘሁ
23
ትራንስ.ረዳት
 
22
መሀመድ በቃ
45
አርሶ አደር
 
23
ረዴላ አወል
19
የታክሲ ረዳት
 
24
ሀብታሙ ኡርጋ
30
ቢዝነስ
 
25
ዳዊት ፀጋዬ
19
መካኒክ
 
26
ገዛኸኝ ገረመው
15
ተማሪ
 
27
ዮናስ አበራ
24
አይታወቅም
 
28
ግርማ ወልዴ
38
ሾፌር
 
29
ደስታ ብሩ
37
ቢዝነስ
 
30
ለገሰ ፈይሳ
60
ቢዝነስ
 
31
ተስፋዬ ቡሽራ
19
ጫማ ጠጋኝ
 
32
ቢንያም ደገፋ
18
ስራ አጥ
 
33
ሚሊዮን ሮቢ
32
ትራንስ.ረዳት
 
34
ደረጀ ደኔ
24
ተማሪ
 
35
ነብዩ ሃይሌ
16
ተማሪ
 
36
ምትኩ ምዋለንዳ
24
ዶመስቲክ ሰራተኛ
 
37
አንዋር ሱሩር
22
ቢዝነስ
 
38
ንጉሴ ዋብግነ
36
ዶመስቲክ ሰራተኛ
 
39
ዙልፋ ሀሰን
50
የቤት እመቤት
 
40
ዋስይሁን ከበደ
16
ተማሪ
 
41
ኤርሚያስ ከበደ
20
ተማሪ
 
42
00428
25
አይታወቅም
 
43
00429 
26
አይታወቅም
 
44
00430 
30
አይታወቅም
 
45
አዲሱ በላቸው
25
አይታወቅም
 
46
ደመቀ አበበ
 
አይታወቅም
 
47
00432 
22
አይታወቅም
 
48
00450 
20
አይታወቅም
 
49
13903 
25
አይታወቅም
 
50
00435 
30
አይታወቅም
 
51
13906 
25
አይታወቅም
 
52
ተማም ሙክታር
25
  
53
በየነ በዛ
25
አይታወቅም
 
54
ወሰን አሰፋ
25
አይታወቅም
 
55
አበበ አንተነህ
30
አይታወቅም
 
56
ፈቃዱ ኃይሌ
25
አይታወቅም
 
57
ኤሊያስ ጎልቴ
 
አይታወቅም
 
58
ብርሃኑ ዋርካ
   
59
አሸብር መኩሪያ
 
አይታወቅም
 
60
ዳዊት ሰማ
 
አይታወቅም
 
61
መርሀጽድቅ ሲራክ
 
አይታወቅም
 
62
በለጠ ጋሻውጠና
 
አይታወቅም
 
63
ብኃይሉ ተስፋዬ
20
አይታወቅም
 
64
21760 
18
አይታወቅም
 
65
21523 
25
አይታወቅም
 
66
11657 
24
አይታወቅም
 
67
21520 
21
አይታወቅም
 
68
21781 
60
አይታወቅም
 
69
ጌታቸው አዘዘ
45
አይታወቅም
 
70
21762 
75
አይታወቅም
 
71
11662 
45
አይታወቅም
 
72
21763 
25
አይታወቅም
 
73
13087 
30
አይታወቅም
 
74
21571 
25
አይታወቅም
 
75
21761 
21
አይታወቅም
 
76
21569 
25
አይታወቅም
 
77
13088 
30
አይታወቅም
 
78
እንዳልካቸው ገብርኤል
27
አይታወቅም
 
79
ኃይለማርያም አምባዬ
20
አይታወቅም
 
80
መብራቱ ዘውዱ
27
አይታወቅም
 
81
ስንታየሁ በየነ
14
አይታወቅም
 
82
ታምሩ ኃይለሚካኤል
 
አይታወቅም
 
83
አድማሱ አበበ
45
አይታወቅም
 
84
እቴነሽ ይማም
50
አይታወቅም
 
85
ወርቄ አበበ
19
አይታወቅም
 
86
ፈቃዱ ደግፌ
27
አይታወቅም
 
87
ሸምሱ ካሊድ
25
አይታወቅም
 
88
አብዱዋሂደ አህመዲን
30
አይታወቅም
 
89
ታከለ ደበሌ
20
አይታወቅም
 
90
ታደሰ ፌይሳ
38
አይታወቅም
 
91
ሶሎሞን ተስፋዬ
25
አይታወቅም
 
92
ቅጣው ወርቁ
25
አይታወቅም
 
93
ደስታ ነጋሽ
30
አይታወቅም
 
94
ይለፍ ነጋ
15
አይታወቅም
 
95
ዮሀንስ ኃይሌ
20
አይታወቅም
 
96
በኃይሉ ብርሀኑ
30
አይታወቅም
 
97
ሙሉ ሶሬሳ
50
አይታወቅም
 
98
የቤት እመቤት  
አይታወቅም
 
99
ቴዎድሮስ
23
አይታወቅም
 
100
ጫማ ሰሪ
 
ጫማ ሰሪ
 
101
በኃይሉ ብርሃኔ
30
አይታወቅም
 
102
ሙሉ ሶሬሳ
50
የቤት እመቤት
 
103
ቴዎድሮስ ኃይሌ
23
ጫማ ሻጭ
 
104
ደጄኔ ይልማ
18
መጋዝን ጠባቂ
 
105
ኡጋሁን ወልደገብርኤል
18
ተማሪ
 
106
ደረጀ ማሞ
27
አናጺ
 
107
ረጋሳ ፈይሳ
55
ላውንድሪ ሰራተኛ
 
108
ቴዎድሮስ ገብረዎልድ
28
የግል ንግድ
 
109
መኮንን ገ/እግዚአብሄር
20
መካኒክ
 
110
ኤሊያስ ገ/ጊዮርጊስ
23
ተማሪ
 
110
አብርሀም መኮንን
21
የቀን ሰራተኛ
 
111
ጥሩወርቅ ገ/ጻድቅ
41
የቤት እመቤት
 
112
ሄኖክ መኮንን
28
አይታወቅም
 
113
ጌቱ ምሀትተ
24
አይታወቅም
 
114
ክብነሽ ታደሰ
52
አይታወቅም
 
115
መሳይ ስጦታው
29
የግል ንግድ
 
116
ሙሉአለም ወይሳ
15
አይታወቅም
 
117
አያልሰው ማሞ
23
አይታወቅም
 
118
ስንታየሁ መለሰ
24
የቀን ሰራተኛ
 
119
ጸዳለ ቢራ
50
የቤት እመቤት
 
120
አባይነህ ሰራሴድ
35
ልብስ ሰፊ
 
121
ፍቅረማርያም ተሊላ
18
ሾፌር
 
122
አለማየሁ ገርባ
26
አይታወቅም
 
124
ጆርጅ አበበ
36
የግል ትራንስፖርት
 
125
ሀብታሙ ዘገየ
16
ተማሪ
 
126
ምትኩ ገ/ስላሴ
24
ተማሪ
 
127
ትዕዛዙ መኩሪያ
24
የግል ንግድ
 
128
ፈቃዱ ዳልጌ
36
ልብስ ሰፊ
 
129
ሸዋጋ ወ/ጊዮርጊስ
38
የቀን ሰራተኛ
 
130
አለማየሁ ዘውዴ
32
የቴክስታይል ሰራተኛ
 
131
ዘላለም ገ/ጻድቅ
31
የታክሲ ሾፌር
 
132
መቆያ ታደሰ
19
ተማሪ
 
133
ሀይልየ ሁሴን
19
ተማሪ
 
134
ፍስሀ ገ/ጻድቅ
23
የፖሊስ ተቀጣሪ
 
135
ወጋየሁ አርጋው
26
ስራ ፈላጊ
 
136
መላኩ ከበደ
19
አይታወቅም
 
137
አባይነህ ኦራ
25
ልብስ ሰፊ
 
138
አበበች ሆለቱ
50
የቤት እመቤት
 
139
ደመቀ ጀንበሬ
30
አርሶ አደር
 
140
ክንዴ ወረሱ
22
ስራ ፈላጊ 141
 
141
እንዳለ ገ/መድህን
23
የግል ንግድ
 
142
አለማየሁ ወልዴ
24
መምህር
 
143
ብስራት ደምሴ
24
መኪና አስመጭ
 
144
መስፍን ጊዮርጊስ
23
የግል ንግድ
 
145
ወሎ ዳሪ
18
የግል ንግድ
 
146
በሀይሉ ገ/መድህን
20
የግል ንግድ
 
147
ሲራጂ ኑሩ ሰይድ
18
ተማሪ
 
148
እዮብ ገ/መድህን
25
ተማሪ
 
149
ዳንኤል ሙሉጌታ
25
የቀን ሰራተኛ
 
150
ቴዎድሮስ ደገፋ
25
የጫማ ፋብሪካ ሰራተኛ
 
151
ጋሻው ሙሉጌታ
24
ተማሪ
 
152
ከበደ ኦርቄ
22
ተማሪ
 
153
ለሊሳ ፋጤሳ
21
ተማሪ
 
154
ጃገማ ባሻ
20
ተማሪ
 
155
ደበላ ጉታ
15
ተማሪ
 
156
መላኩ ፈይሳ
16
ተማሪ
 
157
እልፍነሽ ተክሌ
45
አይታወቅም
 
158
ሀሰን ዱላ
64
አይታወቅም
 
159
ሁሴን ሀሰን ዱላ
25
አይታወቅም
 
160
ደጀኔ ደምሴ
15
አይታወቅም
 
161
ዘመድኩን አግደው
18
አይታወቅም
 
162
ጌታቸው ተረፈ
16
አይታወቅም
 
163
ደለለኝ አለሙ
20
አይታወቅም
 
164
ዩሱፍ ኡመር
20
አይታወቅም
 
165
መኩሪያ ተበጀ
22
አይታወቅም
 
166
ባድሜ ተሻማሁ
20
አይታወቅም
 
167
አምባው ጌታሁን
38
አይታወቅም
 
168
ተሾመ ኪዳኔ
65
የጤና ባለሙያ
 
169
ዮሴፍ ረጋሳ
 
አይታወቅም
 
170
አብዩ ንጉሴ
 
አይታወቅም
 
171
ታደለ በሀጋ
 
አይታወቅም
 
172
ኤፍሬም ሻፊ
 
አይታወቅም
 
173
አበበ ሀማ
 
አይታወቅም
 
174
ገብሬ ሞላ
 
አይታወቅም
 
175
ሰይዴ ኑረዲን
 
አይታወቅም
 
176
እንየው ጸጋዬ
32
እረዳት ትራንስፖርት
 
177
አብዱራህማን ፈረጅ
32
የእንጨት ስራ ባለሙያ
 
178
አምባው ብጡል
60
የቆዳ ፋብሪካ ሰራተኛ
 
179
አብዱልመናን ሁሴን
28
የግል ንግድ
 
180
ጅግሳ ሰጠኝ
18
ተማሪ
 
181
አሰፋ ነጋሳ
33
አናጺ
 
182
ከተማ ኡንኮ
23
ልብስ ሰፊ
 
183
ክብረት እልፍነህ
48
የጥበቃ ሰራተኛ
 
184
እዮብ ዘመድኩን
24
የግል ንግድ
 
185
ተስፋዬ መንገሻ
15
የግል ንግድ
 
186
ካፒቴን ደበሳ ቶሎሳ
58
የግል ንግድ
 
187
ትንሳኤ ዘገየ
14
ልብስ ሰፊ
 
188
ኪዳና ሹክሩ
25
የቀን ሰራተኛ
 
189
አንዷለም ሺበለው
16
ተማሪ
 
190
አዲሱ ተስፋሁን
19
የግል ንግድ
 
191
ካሳ በየነ
28
ልብስ ሽያጭ
 
192
ይታገሱ ሲሳይ
22
አይታወቅም
 
 
የጸጥታ ኃይሎች እርስ በእርስ ባደረጉት የተኩስ ልውውጥ በጥይት የተገደሉ ሰዎች፣
 
193
ነጋ ገብሬ
   
194
ጀበና ደሳለኝ
   
195
ሙሊታ ኢርኮ
   
196
የሃንስ ሶሎሞን
   
197አሸናፊ ደሳለኝ
   
198
ፈይሳ ገ/መንፈስ
   
በመቶዎቹ የሚቆጠሩትን የግድያ ሰለባዎች፣ አካለ ጎደሎዎች፣ ቁስለኞች፣ በኃይል የተመቱትንና ሰውነታቸው በጥይት የተበሳሱትን ሁሉ አስታውሳለሁ፡፡

እ.ኤ.አኖቬምበር 2/2005 ከቃሊቲእስርቤትለማምለጥሲሞክሩበታጣቂዎችበተከፈተተኩስበጥይትተደብድበውያለቁሰዎችስምዝርዝር፣
.
ስም
ጾታ
የተከሰሱበት ጥፋት፣
1
ጠይብ ሸምሱ መሀመድ
ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
2
ሳሊ ከበደ
ምንም ዓይነት ክስ አልተጠቀሰም
3
ሰፊው እንድሪስ ታፈሰ
በአስገድዶ መድፈር
4
ዘገዬ ተንኮሉ በላይ
በዝርፊያ ወንጀል
5
ቢያድግልኝ ታመነ
የተወነጀሉበት ያልታወቀ
6
ገብሬ መስፍን ዳኘ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
7
በቀለ አብርሃም ታዬ
በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
8
ጉታ ሞላ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
9
ኩርፋ መልካ ተሊላ
በማስፈራራት ወንጀል
10
በጋሻው ተረፈ ጉደታ
የህዝብን ሰላም በማደፍረስ ወንጀል
12
አብደልወሃብ አህመዲን
በዘርፊያ ወንጀል
13
ተስፋዬ አብይ ሙሉጌታ
ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
14
አዳነ ቢረዳ
በነፍስ ማጥፋት ወንጀል
15
ይርዳው ከርሴማ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
16
ባልቻ አለሙ ረጋሳ
በዝርፊያ ወንጀል
17
አቡሽ በለው ወዳጆ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
18
ዋለልኝ ታምሬ በላይ
በአስገድዶ መድፈር
19
ቸርነት ኃይሌ ቶላ
በዝርፊያ ወንጀል
20
ተማም ሸምሱ ጎሌ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
21
ገብየሁ በቀለ አለነ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
22
ዳንኤል ታዬ ለኩ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
23
መሀመድ ቱጂ ቀኔ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
24
አብዱ ነጂብ ኑር
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
25
የማታው ሰርቤሎ
በአስገድዶ መድፈር
26
ፍቅሩ ናትናኤል ሰውነህ
በማስፈራራት ወንጀል
27
ሙኒር ከሊል አደም
በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
28
ኃይማኖት በድሉ ተሸመ
ጽንፈኝትን በማራመድ
29
ተስፋዬ ክብሮም ተኬ
በዥርፊያ ወንጀል
30
ወርቅነህ ተፈራ ሁንዴ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
31
ሲሳይ ምትኩ ሁነኛ
በማጭበርበር ወንጀል
32
ሙሉነህ አይናለም ማሞ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
33
ታደሰ ሩፌ የኔነህ
በማስፈራራት ወንጀል
34
አንተነህ በየቻ ቁበታ
ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
35
ዘሪሁን መርሳ
በንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ ወንወጀል
36
ወጋየሁ ዘሪሁን አስፋው
በዝርፊያ ወንጀል
37
በከልካይ ታምሩ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
38
የራስወርቅ አንተነህ
በማጭበርበር ወንጀል
39
ባዝዘው ብርሀኑ
ግብረሰዶም በመፈጸም ድርጊት
40
ሶሎሞን እዮብ ጉታ
በአስገድዶ መድፈር ወንጀል
41
አሳዩ ምትኩ አራጌ
በማስፈራራት ወንወጀል
42
ጋሜ ኃይሉ ዘገዬ
በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
43
ማሩ እናውጋው ድንበሬ
በአስገድዶ መድፈር ወንጀል
44
እጂጉ ምናለ
በግድያ ሙከራ ወንጀል
45
ኃይሉ ቦስኔ ሀቢብ
የተቀደሰን ቦታ በማራከስ
46
ጥላሁን መሰረት
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
47
ንጉሴ በላይነህ
በዝርፊያ ወንጀል
48
አሸናፊ አበባው
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
49
ፈለቀ ድንቄ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
50
ጀንበሬ ድንቅነህ ቢለው
በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
51
ቶሎሳ ወርቁ ደበበ
የዝርፊያ ወንጀል
52
መካሻ በላይነህ ታምሩ
የህዝብን ሰላም በማደፍረስ
53
ይፍሩ አደራው
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
54
ፋንታሁን ዳኘ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
55
ጥበቤ ዋቀኔ ቱፋ
ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
56
ሶሎሞን ገብረአምላክ
የህዝብን ሰላም በማደፍረስ
57
ባንጃው ቹቹ ካሳሁን
በዝርፊያ ወንጀል
58
ደመቀ አበጀ
በግድያ ሙከራ ወንጀል
59
እንዳለ እውነቴ መንግስቴ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
60
አለማየሁ ጋርባ
እ.ኤ.አ በ2004 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አመጽ ጋር በተያያዘ መልኩ በቁጥጥር የዋሉ
61
ሞርቆታ ኢዶሳ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
ለምዘገባ፣ በዚህ እልቂት ላይ ተዋንያን የነበሩ 237 የተረጋገጠ የፖሊስ እና የደህንነት አባላት ዝርዝርን የያዘ ሰነድ ተቀምጧል፡፡
የኔሰው ገብሬን አስታውሳለሁ!
የኔሰው ገብሬ
እ.ኤ.አ በ11/11/11 የኔሰው ገብሬ የተባለ የ29 ዓመት መምህር እና የሰብአዊ መብት ተሟጋች በደቡብ ኢትዮጵያ በዳውሮ ዞን በተርጫ ከተማ ከህዝብ መሰብሰቢያ ዳራሽ ፊት ለፊት እሳት በመለኮስ እራሱን በእሳት አያይዟል፡፡ ለሶስት ቀናት ቆስሎ ከቆየ በኋላ ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል፡፡ እራሱን በእሳት ከማያያዙ በፊት የኔሰው ከህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውጭ ለተሰበሰበ ህዝብ እንዲህ የሚል ንግግር አሰምቶ ነበር፣ “በእኩልነት ላይ ባልተመሰረተ አስተዳደር እና ፍትህ በሌለበት እንዲሁም የሰብአዊ መብት በማይከበርበት አገር ውስጥ እራሴን ለመስዋዕትነት አቀርባለሁ፣ ይህንንም በማድረጌ ወጣቱ ትውልድ ነጻ ይወጣል፡፡” የአትዮጵያ ጀግናዉ የእኔሰው ገብሬን አስታውሳለሁ
“ገዳዮችን አስታውሳለሁ፣ የግድያ ሰለባዎችንም አስታውሳለሁ፣ ለትግሌ የሚያግዙ አንድ ሺ እና ከዚያ በላይ ያሉ አሳማኝ ምክንያቶች እና ተስፋ ቢኖረኝም፡፡ ባስታወስኩ ቁጥር ተስፋየ ይሟጠጣል፣ ያንን ድርጊት ባስታውስኩ ቁጥር ደግሞ ተስፋቢስነቴን የማስወገድ ኃላፊነት እንዳለብኝ እገነዘበላሁ፣ ተስፋ ከተስፋቢስነት በላይ ነው፡፡“ ይላል ኤሊ ዊሴል!
**ለጥቃቱ ሰለባዎች ተጨማሪ መረጃ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆኑት ያሬድ ኃ/ማርያም እ.ኤ.አ ሜይ 15/2006 በሰው ልጆች ላይ የተፈጸመ  ወንጀል በኢትዮጵያ፣ የጁንና ኖቬምበር 2005 የአዲስ አበባው ዕልቂት በሚል ርዕስ ለአውሮፓ ህብረት ፓርላሜንት ለልማትና ውጭ ጉዳዮች እና ለሰብአዊ መብቶች ንዑስ ኮሚቴ አስቸኳይ ጥምር ጉባኤ የቃረቡትን ምስክርነት ይመለከቷል፡፡
***የመርማሪ ኮሚሽኑ ሪፖርት ሙሉ በሙሉ የጥቃቱ ሰለባዎችን ነጻ ሲያወጣ አጠቃላይ ኃላፊነቱን ግን በፖሊስና ታጣቂ ኃይሎች ላይ ደፍድፎታል፡፡ መርማሪ ኮሚሽኑ አስተያየቱን በመቀጠል እንደሚከተለው አጠቃሎታል፣ “በተቃዋሚዎቹ የተጎዳ ንብረት የለም፣ በመንግስት በሞኖፖል በተያዘው መገናኛ ብዙሀን እንደተለፈፈው ጥቂት ተቃዋሚዎች የእጅ ቦንቦችንና ጠመንጃዎችን ታጥቀዋል እንደሚለው ሳይሆን በተቃራኒው የእጅ ቦንብ እና ጠብመንጃ የታጠቀ አንድም የተቀዋሚ አባል የለም፣ በመንግስት ታጣቂ ኃይሎች የተከፈተው ተኩስ ሰላማዊ ሰልፈኞችን ለመበተን ሳይሆን በተቃራኒው የሰልፈኞችን ጭንቅላትና ደረት ለመበርቀስ ዒላማ ያደረገ ነበር፡፡” የመርማሪ ኮሚሽኑ የ193 የእልቂቱ ሰለባዎችን ስም ዝርዝር የያዘ ሰነድ የሚያካትተው እ.ኤ.አ ከጁን 6 – 8 እና ከኖቬምበር 1- 4/2005 በዚህ ጊዜ ብቻ ያለውን ድርጊት እንዲያጣራ ለአጣሪ ኮሚሽኑ የተሰጠው ስልጣን ነበር፡፡ አጣሪ ኮሚሽኑ ግን በፓርላማው ከተሰጠው የጊዜ ገደብ ውጭ ከህግ ውጭ በመንግስት የፖሊስና የደህንነት ኃይሎች የተፈጸሙ ግድያዎችን ስም ዝዝዝር ያገኘ ቢሆንም እነዚህ ግድያዎች ኮሚሽኑ እንዲያጣራ ተለይቶ ከተሰጠው ጊዜ ውጭ በመሆናቸ ለህዝብ ይፋ ሳያደርገው ቀርቷል፡፡

No comments:

Post a Comment