Monday, January 27, 2014





Norway coordinators for the 24 jan 2014 ethiopians worldwide demonestration
ሰው ይናፍቀኛል

አገሩን የሚወድ በእውነተኛ ፍቅር
ነገን የሚመለከት በትናንት የማይኖር
ሰውን በሰውነት ዘወትር የሚያከብር
ሰው ይናፍቀኛል ለሰው ልጅ የሚኖር
ክፋት ምቀኝነት ተንኮል የሌለበት
ልቡ በጥላቻ ያልተሸነፈበት
በዘመን መካከል የማይለዋወጥ
የኋላውን ረስቶ ወደ ፊት የሚሮጥ
ሁሌ ሰው ያምረኛል ፍቅር የሚሰጠኝ
በደካማ ጎኔ ቆሞ የሚረዳኝ
ሳጠፋ የሚመክረኝ በቅንነት መንፈስ
ድካሜን የሚሸከም ብርታቴን የሚያወድስ
ሰው ይናፍቀኛል ሰውን የሚያፈቅር
ወደ ፊት እያየ በትናንት የማይኖር
በትዕግስት እንድሮጥ አቅም የሚሆነኝ
ችግሬን ተጋርቶ ደስታ የሚሰጠኝ
ህልሜን የሚፈታ ምኞቴን የሚካፈል
ጉልበቴ ሲደክም ሸክሜን የሚያቃልል
በፍቅር እየኖረ ፍቅር የሚያስተምረኝ
ሰው ይናፍቀኛል ሁሌ የሚኖር አብሮኝ
አማራ ነህ ትግሬ ወይስ ነህ ኦሮሞ
እያለ የማይጮህ ከምባታና ጋሞ
ነፍሴን የማያዝል በነገር ቡትቶ
ሰው ይናፍቀኛል ሰው የሚሆን ሰርቶ
በጥላቻ የማይኖር ፍቅር የበዛለት
ለአገር ለወገኑ የሚኖር በቅንነት
በአዲስ አስተሳሰብ ነፍሱ የተሞላ
በዘረኝነት መርዝ ጉልበቱ ያልላላ
ሁሌ የሚመለከት በፍቅር መነፅር
ያለውን አካፍሎ ለወገኑ የሚኖር
ሰው ይናፍቀኛል ነገን የሚያሳየኝ
በኢትዮጵያዊነት ልቤን የሚገዛኝ።

ጥር 19 ቀን 2006 ዓ•ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በቅርብ እውን ይሆናል!!!

ሂውማን ራይትስ ዎች በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩ ይበልጥ ጠቧል


መንግስት፤ ተቋሙ የተቃዋሚዎች የፕሮፖጋንዳ ማስፈፀሚያ ነው
“በኢትዮጵያ የነፃ ሚዲያ ህልውና አደጋ ላይ ነው”
“በኤርትራ የመብት ጥያቄ ማንሳት ነውር ሆኗል” ብሏል
የኢትዮጵያ መንግስት የዜጐችን  ሰብአዊ መብት በስፋት ይጥሳል በማለት ተደጋጋሚ ወቀሳና ስሞታ የሚያቀርበው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘው አለማቀፍ የመብት ተቋም፤  ሰሞኑን ይፋ ባደረገው አመታዊ ሪፖርቱ፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ነፃነት ይበልጥ መጥበቡንና የነጻ ሚዲያ ህልውና አደጋ ላይ መውደቁን ገለፀ፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ፤ የተቋሙን ሪፖርት ያጣጥላል፡፡ በአገሪቱ ውስጥ የፖለቲካ ነፃነትና የፖለቲካ እንቅስቃሴ የማካሄድ እድል (የፖለቲካ ምህዳር) እየጠበበ የመጣው ከምርጫ 97 በኋላ መሆኑን የገለፀው ሂውማን ራይትስ ዎች፤ ከዚያ ወዲህ በመንግስት የፀደቁትን የፀረ – ሽብር እና የበጐ አድራጐት ማህበራት አዋጆችን በምሳሌነት ጠቅሷል፡፡ በፀረ – ሽብር አዋጁ መነሻነት ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች ሽብርተኛ ተብለው እንደታሠሩና እንደተፈረደባቸው የተቋሙ ሪፖርት ጠቅሶ፣ በህጋዊና ሰላማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፍርሃት እንዲሸበቡ ተደርገዋል ብሏል፡፡
ጋዜጠኞች የፀረ-ሽብር አዋጁን በመፍራት የሙያ ተግባራቸውን እንዳያከናውኑ መታፈናቸውን ሲገልጽም፤ የአዋጁ አንቀፅ እየተጠቀሰ እሥራት የተፈረደባቸው ጋዜጠኞች መኖራቸውንም አውስቷል፡፡
በኢትዮጵያ ጐልተው የሚታዩት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የፖለቲካ ምህዳር መጥበብና የኘሬሶች አፈና ቢሆኑም፤ ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችም መሻሻል አላሣዩም ብሏል ሪፖርቱ፡፡
በማረሚያ ቤት ያሉ እሥረኞች በገለልተኛ አካላት እንዳይጐበኙ መከልከል፣ ያልተፈረደባቸው ግለሰቦችን አስሮ ማቆየትና ለፍርድ ቤት አቤቱታ እንዳይቀርቡ ማገድ፤ ያልተፈረደባቸውን ሰዎች በብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሚሠራጩ ፕሮግራሞች ላይ እንደ ወንጀለኛ መፈረጅ… በአገሪቱ ከሚታዩ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ውስጥ የሚካተቱ መሆናቸውን ሪፖርቱ ዘርዝሯል፡፡
ሠላማዊ ሠልፍ የማካሄድ፣ የመብት ጥያቄ የማቅረብና ተቃውሞን የማሰማት መብቶችንም ፈትሼያለሁ የሚለው ሂውማን ራይትስ ዎች፤ ጥያቄ ባቀረቡና ሰላማዊ ሰልፍ ባካሄዱ ሙስሊሞች ላይ እንግልት፣ ድብደባና እሥር ተፈጽሟል ብሏል፡፡ በተቃዋሚ ፓርቲዎች የተጠሩ ሠላማዊ ሠልፎችም  በአፈና ውስጥ የተካሄዱ መሆናቸው በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡
በአለማቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የመብት ጥሰት ይፈጸምባቸዋል ከተባሉት አገራት መካከል ኤርትራ በቀዳሚዎቹ ተርታ ውስጥ እንደምትመደብ ተቋሙ ገልፆ፤ ጋዜጠኞች ለእሥራት እና ለእንግልት፤ ብዙ ዜጐችም ለስደት መዳረጋቸውን ዘርዝሯል፡፡
በኤርትራ የመብት ጥያቄ ማንሣት ነውር ሆኗል ያለው ይሄው ሪፖርት፤ የኤርትራ ሁኔታ ከሁሉም የአፍሪካ ሀገራት እጅግ በጣም አሣሣቢ ነው ብሏል፡፡
ሃሣብን በነጻነት መግለጽ፣ መደራጀትና የፈለጉትን አቋም መያዝ ለኤርትራውያን እንደማይፈቀድ በመጥቀስም፤ ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጪ ሰዎች እየተያዙ ይታሠራሉ፤ እስር ቤት የታጐሩ  ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞችና ሌሎች ዜጐች  ያለምንም ፍርድ ከ10 ዓመት በላይ ሆኗቸዋል ብሏል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት ሂውማን ራይትስ ዎች የሚያወጣቸውን ሪፖርቶች ሙሉ ለሙሉ እንደማይቀበል በተደጋጋሚ ያስታወቀ ሲሆን፤ ተቋሙ ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት የሚሠራ ነው፤  የተቃዋሚ ሃይሎች የኘሮፖጋንዳ ማስፈጸሚያ ነው ሲል ይከሳል፡፡
ሰሞኑን የተሰራጨውን አመታዊ ሪፖርት በተመለከተ የጠየቅናቸው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል፤ “ሂውማን ራይትስ ዎች የሚያወጣው ሪፖርት ተአማኒነት የሌለውና ገጽታን ለማጠልሸት ያለመ ነው” ብለዋል፡፡
ተቋሙ ሀገር ውስጥ ሣይገኝ ወይም መርማሪዎቹን ሣይልክ፣ ኬንያናና ሌላ ሀገር ተቀምጦ ከተቃዋሚዎች በሚቃርመው ያልተጣራ ተባራሪ ወሬ ላይ ተመስርቶ፣ ከመንግስት ምላሽ ሳይጠይቅ የሚያወጣው መናኛ ሪፖርት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ፈጽሞ አይገልጽም ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታው፡፡
ተቋሙ የኢትዮጵያን መንግስት ለማጥላላት  አቅዶ የሚሠራ ነው ያሉት አቶ ሽመልስ፤ የተቋሙ የምስራቅ አፍሪካ ወኪል አቶ ዳንኤል በቀለ፣ ህገ-መንግስቱን የማፍረስ ነውጥ በማስነሳት የተከሰሱና የተፈረደባቸው፣ ይቅርታ ጠይቀው ቢለቀቁም በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ቂም የቋጠሩ በመሆናቸው ሪፖርታቸው ገለልተኛ ሊሆን አይችልም ብለዋል። ይህ ሲባል ግን ሀገራችን ታዳጊ ሀገር እንደመሆኗ ችግሮች አይኖሩም ማለት አይደለም ያሉት ኃላፊው፤ የኘሬስ ነጻነትና የጋዜጠኞች መብት ሙሉ ለሙሉ ተጠብቆ ኘሬሱ እንዲጠናከርና  እንዲስፋፋ እየተደረገ ነው፣ ከባለሙያዎች ጋርም እየተመካከርን በጋራ እየሠራን ነው ብለዋል፡፡

በሰማያዊ ፓርቲ ስም አመሰግናለሁ! (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)


ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
ባለፉት በርካታ ሳምንታት በተናጠል እና በቡድን እየሆናችሁ በአሜሪካ እና በአውሮፓ የተለያዩ ከተሞች የስብሰባ አዳራሾች በመገኘት ለሰማያዊ ፓርቲ ድጋፋችሁን ላደረጋችሁ ወገኖቼ ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ!Semayawi party chairman Engineer Yilkal Getnet's Washington D.C. meeting.
ባለፈው ሳምንት ኢትዮሜዲያ/Ethiomedia.com የተባለው ድረገጽ ባወጣው ዘገባ መሰረት ሰማያዊ ፓርቲ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ባለው የፖለቲካ ትግል ሂደት “አዲስ የተቃውሞ ኃይል” ሆኖ በመቅረብ ሰላማዊ የስርዓት ለውጥ ሽግግር ለማምጣት “አዲስ ተስፋን ፈንጣቂ” ሆኗል በማለት ገልጾታል፡፡ ወጣቱ እና መንፈሰ ጠንካራው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በተለያዩ የአሜሪካ እና የአውሮፓ ከተሞች በመዘዋወር በተስፋ፣ በሰላም እና በአንድነት መሰረት ላይ ፍቅር የነገሰባት አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት ሰማያዊ ፓርቲ ያለውን ራዕይ ለኢትዮጵያውያን/ት ግልጽ አድርጓል፡፡
እ.ኤ.አ ዴሴምበር 15/2013 በሰሜን አሜሪካ በአርሊንግተን ከተማ የመጀመሪያው ስብሰባ በተደረገበት ዕለት ይልቃል ለስብሰባው ታዳሚዎች ወደ አሜሪካ የመጣሁት ገንዘብ ለማሰባሰብ ወይም ገንዘብ ለመጠየቅ ሳይሆን ወደዚህ የመጣሁበት ዋናው ምክንያት የሰማያዊ ፓርቲን ራዕይ፣ አቋም እና ፕሮግራም፣ እንዲሁም ፓርቲው በተቋቋመ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ያከናወናቸውን በርካታ ተግባራት እንዲሁም ፓርቲውን አስመልክቶ ለሚነሱ ጥያቄዎች እና ማብራሪያ ለሚጠይቁ ጉዳዮች እዚህ ለሚኖሩት ኢትዮጵያውያን/ት ወገኖቼ ለማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ለማስጨበጥ ነው ብሏል፡፡ የፓርቲው አፈቀላጤ በመሆን ፓርቲውን በማስተዋወቅ ረገድ እጅግ ስኬታማ ስራ አከናውኗል፡፡ የቀረቡለትን ሁሉንም ጥያቄዎች ምንም የሚያደናግር ነገር ሳይጨምር ወይም ግልጽ በሆነ መልክ ለታዳሚው አብራርቷል፡፡ የፖሊሲ ጉዳዮችን በጥንቃቄ እና አርቆ አስተዋይነትን ባካተተ መልኩ ምላሽ በመስጠት ለማስተናገድ ሞክሯል፡፡ ለታዳሚዎች ያቀረባቸው ገለጻዎች የተሟሉ እና  የሁለተኛ ደረጃ መረጃ ምንጮች ሆነው በሀአዝ የተደገፉ መረጃዎች ነበሩ፡፡ ልዩ በሆነ አመክንዮአዊ ገለጻ እና የተሳታፊውን ቀልብ በሚገዛ አንደበተ ርዕቱ የቋንቋ አቀራረብ የታዳሚውን አውድ ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮት ነበር፡፡ በዚህ ፓርቲውን በማስተዋወቅ የጉዞ ሂደት ጊዜ ከሰማያዊ ፓርቲ እና ከይልቃል ጎን በመሰለፍ ቀጣይነት ያለውን የበኩሌን ድጋፍ በማድረጌ ታላቅ ኩራት ይሰማኛል፡፡
ለሰማያዊ ፓርቲ የሞራል ድጋፍ እና የገንዘብ እርዳታ ላደረጋችሁ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ፣ በአትላንታ፣ በሀውስተን፣ በዳላስ፣ በሳንጆሴ፣ በሎስአንጀለስ፣ በላስቬጋስ እና በሲያትል ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ወገኖቼ በሙሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናየን ላቀርብላችሁ እወዳለሁ፡፡ ሁላችሁንም አመሰግናለሁ፣ በእናንተ ኮርቻለሁ!
በሰሜን አሜሪካ ከተሞች ለሰማያዊ ፓርቲ በተዘጋጁት የስብሰባ መድረኮች ላይ ለተገኛችሁ፣ ስብሰባውን በአንክሮ በመከታተል ለተሳተፋችሁ፣ ጠንካራ ጥያቄዎችን በማቅረብ ተሳትፏችሁን ላደረጋችሁ እና ለፓርቲው ህልውና ማጠናከሪያ የገንዘብ ድጋፍ ላደረጋችሁ ኢትዮጵያውያን/ት ወገኖቼ ሁሉ በሰሜን አሜሪካ የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ሰጭ ቡድን ስም ታላቅ ምስጋና አቀርባለሁ፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ዝናቡን፣ ደመናውን፣ በረዶውን እና ጨለማውን በጽናት በመቋቋም ስብሰባዎችን ለተሳተፋችሁ እና የማይታጠፈውን ድጋፋችሁን ላደረጋችሁ የፓርቲው አባላት እና ንቁ ደጋፊዎች በሙሉ በሰማያዊ ፓርቲ ስም ላቅ ያለ ምስጋናዬን ላቀርብ እወዳለሁ፡፡ የእናንተ ድጋፍ ታላቅ ለውጥ አስገኝቷል፣ ወደፊትም ያስገኛል፡፡
የሰማዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ይልቃልን ለመጀመሪያ ጊዜ የአሜሪካን ጉብኝቱን በማስመልከት አጠቃላይ የተሰማውን ስሜት እንዲገልጽልኝ ላቀረብኩለት ጥያቄ ሊገልጸው ከሚችለው በላይ እንደተደሰተ እንዲሁም ለወገኖቹ ከፍተኛ ምስጋና እና አድናቆት ያለው መሆኑን ገልጿል፡፡ በየቦታው ባገኛቸው ስለሀገራቸው ፍቅር እና ጅግንነት የተሞላበት ስሜት በሚያንጸባርቁ ኢትዮጵያውያን/ት ስሜት እጅግ ተደምሟል፡፡ በእነርሱ ከልብ የመነጨ የአገር ወዳድነት ስሜት በመመሰጥ ለወደፊቷ አዲሲቷ ኢትዮጵያ መመስረት የበለጠ ጥልቅ ስሜት እንዲኖረው አድርጎታል፡፡ እንዲሁም የኢትዮጵያ ወጣቶችን ለመርዳት የሰጧቸውን ምክሮች እና ያደረጓቸውን ውይይቶች በተመስጦ አዳምጧል፡፡ ይልቃል በዚህች አጭር ጊዜ ውስጥ በአሜሪካ ለሰማያዊ ፓርቲ ለተደረገው ከፍተኛ እርዳታ እና እገዛ ብቻ አይደለም ከፍተኛ ምስጋናውን ያቀረበው እና የተደነቀው፣ ሆኖም ግን በኢትዮጵያውያኑ/ቱ መከባበር፣ ፍቅር እና በሁሉም ዘንድ ስላስተዋለው መናበብ ጭምር እንጂ፡፡
ጉብኝቱ የሚፈጥራቸው ስዕሎች፣
የሰማያዊ ፓርቲ የአንድ ጊዜ ጉብኝት ትምህርታዊ፣ ቀስቃሽነት፣አረጋጋጭነት፣ እና ስሜታዊነት የተንጸባረቀበት ልምድ መስሎ ሊታየን ይችላል፡፡ ለእኔ የጉዞው ጉብኝት “የእውነት ድርጊቶች“ ማቀነባበሪያ ትውስታ ሆኖ ይታየኛል፡፡ እኔ ስለኢትዮጵያ ወጣቶች እና ስለታሪካዊ ዕጣፈንታቸው ከብዙ ጊዜ ጀምሮ እናገር እና እጽፍ ነበር፡፡ ያ ህልም አሁን እውን ሆኖ በፖለቲካ ድርጅት ማቋቋም (በእኔ እምነት የወጣቶች ንቅናቄ) የተከሰተ ሲሆን ይህም የወጣቶች፣ ለወጣቶች፣ በወጣቶች የተመሰረተ ፓርቲ ነው፡፡ ከዚህም በላይ በአሁኑ ጊዜ ከኢትዮጵያ ህዝብ እድሜው ከ35 ዓመት በታች የሚሆነውን 70 በመቶ የያዘው የወጣቱ ህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡
የኢትዮጵያ አቦ-ጉማሬው ትውልድ (የቀድሞው ትውልድ) አባል ሆኘ ከኢትዮጵያ የአቦሸማኔው ትውልድ (ወጣቱ ትውልድ) ጋር ተቀራርቦ የመስራት ዕድሉን በማግኘቴ ታላቅ ክብር እና ሞገስ ይሰማኛል፡፡ እነዚህ የወጣቱ ትውልድ አባላት አስደናቂዎች ናቸው፡፡ በአእምሯቸው ፈጣንነት፣ በአስደናቂ እይታቸው እና አመለካከታቸው፣ እርምጃ ለመውሰድ ባላቸው መንፈሰ ጠንካራነት፣ የቴክኖሎጅ እድገትን ለማምጣት ባላቸው በጎ አመለካከት እና ብቃት፣ በቴክኒክ እና በድርጅታዊ ክህሎት ፈጣን ችሎታቸው እና መግባባትን በተላበሰ መልክ በሚያደርጓቸው የስራ ግንኙነቶች በጣም እደነቃለሁ፡፡ አቦሸማኔውን (እራሴን “የአቦ-ጉማሬው ትውልድ” አባል አድርጌ ብቆጥረውም ቅሉ የመካከለኛው ትውልድ አባል ዋና ተግባሩ የአቦሸማኔውን እና የጉማሬውን ትውልዶች የሚያገናኙ ድልድዮችን መገንባት) በምክር እና በሀሳብ ማገዝ፣ የምክር አገልግሎት መስጠት፣ ጥያቄዎችን መመለስ እና በተፈለግሁበት ጊዜ ሁሉ እየተገኘሁ ስለሰማያዊ ፓርቲ አስረጅነት ምስክርነቴን የመስጠት ሚና ከልብ የምደሰትበት ተግባር መሆኑ ላይ ሙሉ እምነት አለኝ፡፡
በሰማያዊ ፓርቲ የጉብኝት ጉዞ ጊዜ ያለንን የጋራ ስብስብ ልምዶች በተሻለ መልክ የሚገልጸው አንድ ቃል “መከባበር” የሚለው ነው፡፡ ፍቅር እና መተባበርን በተላበሰ መልኩ ሁሉንም ዜጎቿን በእኩልነት እና የእያንዳንዱን ዜጋ መብት እና ክብር በሚጠብቅ ግንኙነት ላይ ተመስርቶ ፍቅር የነገሰባትን አዲሲቷን ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ ኢትዮጵያውያን/ት በየሄድንበት ሁሉ ከልብ በመነጨ መልክ ሲያደርጉት የነበረው ተሳትፎ እና አቀባበል ስሜታችንን ገዝቶ ከልብ እንድንመሰጥ አድርጎናል፡፡ ኢትዮጵያውያንን/ትን በመከፋፈል እና ከሰብአዊነት በማውረድ በጎሳ፣ በኃይማኖት፣ በክልል እና በቋንቋ በመለያየት የሚያራምደውን ስርዓት በመቃወም ሀሳባቸውን በግልጽ ሲያራምዱ በነበሩት ኢትዮጵያውያን/ት ወገኖቻችን ከልብ ተመስጠናል፡፡ ካለፉት ስህተቶች እንድንማር እና በትግል ሂደቱ ወቅት በውል ተለይተው የሚታወቁ ስህተቶችን ልናስወግድ የምንችልባቸውን መንገዶች እንድንገነዘብ ገንቢ የሆነ ምክራቸውን ሲሰጡን ለነበሩት ወገኖቻችን ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ ውድቀትን እራሱን በምንም ዓይነት መንገድ እንዳንፈራ፣ ሆኖም ግን ውድቀትን መፍራት ሽባ እና አቅመቢስ እንደሚያደርገን ፍቅር የተላበሱት ወገኖቻችን አጽንኦ በመስጠት የመከሩን ምክር በልባችን ሰርጾ በደምስራችን ሁሉ ተዋህዶ እንድንደፋፈር እና በሞራል እንድንሞላ ስንቅ ሆኖናል፡፡ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት ለምናደርገው ትግል የቱንም ያህል ጊዜ ቢወስድም ከጎናችን በመቆም ትግሉን በሞራል፣ በገንዘብ እና በማቴሪያል ለማገዝ ቃል በገቡልን ወገኖቻችን እጅግ ተደስተናል፡፡ ቅንነት በተሞላበት መንፈስ ስለሰማያዊ ፓርቲ ምንነት ከአንዳንድ ወገኖቻችን የበለጠ ለማወቅ እና ከጎኑ ለመሰለፍ እንዲችሉ ለማድረግ የነበረው ጉጉት እና ሲንጸባረቅ የነበረው የተነሳሽነት ስሜት በደስታ እንድንሞላ አድርጎናል፡፡
በጉብኝት ጉዞው ጊዜ ባካሄድናቸው በአንዳንድ የስብሰባ ቦታዎች በወገኖቻችን የተነሱ ጥቂት ጨለምተኝነት የተንጸባረቀባቸው ስሜቶችንም በማስታወሻችን ከትበን ይዘናል፡፡ አንዳንዶቹ ተስፋ በቆረጠ መልኩ ብሩህ ነገር እንደማይታያቸው የሰጡት አስተያየት ከእውነታው ውጭ እንደሆነ ስለምናምን እንድናዝን አድርጎናል፡፡ ምክንያቱም አንድ ጊዜ ወይም ሁለት ጊዜ ካልተሳካ በሌላ ጊዜም አይሳካም የሚል ሃይማኖታዊም ሆነ ሳይንሳዊ አመክንዮ የለም፡፡ ጨለምተኝነታቸውን የበለጠ ለማስረገጥም እንዲህ ብለዋል፣ “ከእናንተ በፊት ሁሉም ወደ እኛ የመጡት ሁሉ ስኬታማ ሳይሆኑ ቀርተዋል፣ የእናንተስ እጣፈንታ ከዚያ የማይለይ ላለመሆኑ ምን ማረጋገጫ አለን? እናንተም ስኬታማ ላለመሆን ትችላላችሁ“ በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ ይህን በማለት ያቀረቧቸውን ቅሬታቸው በሚገባ እንረዳለን፡፡ ሌሎቹ እብሪት አዘል አስተሳሰብ የያዙ ወገኖቻችን ደግሞ የወጣቶችን የብሩህ አእምሮ ባለቤትነት እና የአዳዳስ ሀሳቦች አፍላቂ እና ፈጣሪዎች ስብዕናን አሳንሶ በማየት  ወጣቶቹ ምን እንደሚሰሩ አያውቁም በማለት እንደሚያስቡ እና ወጣቶቹ ምን መስራት እንዳለባቸው እና መስራት እንደሌለባቸው ለመስበክ ሲሞክሩ ስንሰማ በጣም አስገርሞናል፡፡ እኛ ለዚህ ግድ የለንም፡፡ ምንጊዜም ለመማር ዝግጁ ነን፡፡ እንዲህ በሚሉት የቶማስ ጥርጣሬዎች ተይዘን ነበር፣ “ሲመጡ እና ሲሄዱ አይተናል፣ ከሌሎች የተለዬ ሆናችሁ የምትታዩበት ነገር የለም፣ እናንተን ልዩ የሚያደርጋችሁ የሚለያችሁ ነገር ምንድን ነው?“ ለጉዳዩ ትኩረት ባለመስጠት ትንሽ የንቀት ስሜት በተቀላቀለበት አኳኋን ሲጠይቁ ነበር፡፡ ጥርጣሬ የእምነት መሰረት ነው፡፡ ፍቅር የነገሰባት አዲሲቷ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ወጣት የህብረተሰብ ክፍል ተዋናይነት በእርግጥም በቀድሞው ትውልድ ድጋፍ ትገነባለች በማለት እነርሱን ለማሳመን ማድረግ ያለብንን ሁሉ አድርገናል፡፡ ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ የሆድ ቁርጠት የሆነባቸውን፣ የደስታ ስሜት የራቃቸውን፣ የሚያጉረመርሙትን እና የሚያማርሩትን ወገኖቻችን ትዕግስት በተሞላበት ሁኔታ እና በከበሬታ አዳምጠናቸዋል፡፡ ይህንንም ለማድረግ በቂ ምክንያቶች ነበሯቸው፡፡
ከዚህም በተጨማሪም ስለእራሳችን እና ምን ማድረግ እንዳለብንም ተምረናል፡፡ የትግል ስልታችንን ማስረዳት እና መግለጽ ነበረብን፡፡ እንዲህ የሚል ጥያቄም ቀርቦልን ነበር፣ “እስከ አፍንጫው ድረስ የጦር መሳሪያ የታጠቀ እና በፖሊስ እና በደህንነት ኃይል የተደራጀ ጨካኝነት የተሞላበት ታሪክ ያለው አምባገነን ገዥ አካል ድል ለማድረግ እንዴት ይቻላል ብላችሁ ታስባላችሁ?“ የእኛ መልስ ጋንዲ ከሰጡት መልስ ጋር ተመሳሳይ ነበር፣ እንዲህ የሚል፣ “ጥንካሬ ከአካላዊ ብቃት የሚመጣ አይደለም፣ ወይም ደግሞ ከጠብ መንጃ፣ ከታንክ እና ከጦር አውሮፕላን የሚመጣ አይደለም፣ ጥንካሬ ወዲያውኑም ድል የሚመጣው ከማይበገረው ጽኑ  እምነታችን ነው፡፡“ በሰላማዊ ትግላችን ላይ ማህለቁን የጣለ የማይበገር ጽኑ እምነት አለን፡፡ በፍቅር የተሞላ የማይበገር ጽኑ እምነት ምንጊዜም ሊሸነፍ አይችልም፡፡
ምንጊዜም ቢሆን ለውጥ በአጠቃላይ በህብረተሰቡ ውስጥ ከመምጣቱ በፊት በእያንዳንዱ ወንድ እና ሴት ልብ እና አእምሮ ውስጥ መስረጽ እንዳለበት አስተምረናል፡፡  ስለዚህም እኛን ጥላሸት ለመቀባት ከሚፈልጉት ወገኖቻችን ጋር ትግል ከመጀመራችን በፊት በልቦቻችን ውስጥ ኑሮን ከመሰረቱት ከጥላቻ እና ከበቀል ጭራቆች ጋር ትግላችንን ማድረግ ይኖርብናል፡፡ ከእኛ ሀሳቦች፣ የማስፈጸሚያ መንገዶች እና ስልቶች ጋር ከማይስማሙ ወገኖቻችን ጋር ትዕግስት እና መከባበርን በተላበሰ መልኩ ልናስተናግድ ይገባል፡፡ በመርህ ደረጃ ምንጊዜም በመሬት ላይ መቆም አለብን፡፡ በሰላማዊ የማህበራዊ እና የፖለቲካ ለውጥ እናምናለን፡፡ በዚህ መርህ መሰረት ከማንም ጋር ቢሆን ካለመስማማት ውጭ ካልሆነ በስተቀር ላለመስማማት መስማማት ይኖርብናል፡፡  በሌሎች ስኬቶች እና ስህተቶች ሳይሆን እኛ በምናበረክተው ጠቀሜታ ብቻ መገምገም እንዳለብን እናምናለን፡፡ የምንለውን በተግባር ላይ ለማዋል ምንጊዜም ቢሆን ጠንቃቃ መሆን አለብን፡፡ ይህም ማለት ከፍተኛ የሆነ የተያቂነት፣ የግልጽነት እና የሰለጠነ አካሄድ ስርዓትን መከተል ይኖርብናል፡፡ በእርግጥ ደጋፊዎቻችን የእኛን ልዩ ሆኖ መቅረብ፣ የበለጠ ታማኝነትን እና ቀጥተኛነትን ማሳየት እና ሀሳቦችን ለመቀበል ዝግጁ ሆኖ መገኘት እንዳለብን ከእኛ ይጠብቃሉ፡፡
የወደፊት ትግላችን፡ ኢትዮጵያ እንደ ዳዊት እና ህወሀት/ኢህአዴግ እንደ ጎልያድ
በኢትዮጵያ የሚደረገው የስርዓት ለውጥ በጣም አስቸጋሪ እና ታላቅ መስዋዕትነትን የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡ ገዥው አካል ሰማያዊ ፓርቲን ለማዳከም እና ለመደምሰስ ሲል ያለውን ኃይል ሁሉ በመጠቀም ሌት እና ቀን እንደሚሰራ ለእኛ የሚሰወር አይደለም፡፡ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ገዥው አካል በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ በዘፈቀደ ከህግ አግባብ ውጭ በቁጥጥር ስር የማዋል፣ የእስራት፣ የማሰቃየት፣ የይስሙላ የህግ ሂደትን የማሳየት እና የግድያ ተግባራትን ሊፈጽም እንደሚችል ከግንዛቤ ማስገባት ይኖርብናል፡፡ ገዥው አካል በሰማያዊ ፓርቲ አባላት እንቅስቃሴ ላይ ህገወጥ እርምጃ ሊፈጽም እንደሚችል መተንበይ ማለት ነገ ፀሐይ ትወጣለች ብሎ እንደመተንበይ ይቆጠራል፡፡ ላለፉት 23 ዓመታት ገዥው አካል እየተከተለ ያለውን የአሰራር ተሞክሮ እናውቃለን፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች እና አባላት በምንም ዓይነት መልኩ አይፈሩም፡፡ የሰለጠኑ ወሮበላ ደብዳቢዎችን እና ጠመንጃዎችን አይፈሩም፡፡ በአሁኑ ጊዜ አዲስ ዝርያ ያላቸው ኢትየጵያውያን/ት ወጣት መሪዎች እየተነሱ እና ለነጻነት እና ለዴሞክራሲ ከፍተኛ ተጋድሎ እያደረጉ ያለበት ሁኔታ እየተፈጠረ ስለሆነ ባለው ገዥ አካል ካባ ስር ተደብቀው እና ተወሽቀው በሰላማዊ ዜጎች ላይ ሸፍጥ በመስራት ላይ ያሉትን ወሮበሎች የሚፈሩ አይደሉም፡፡ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ ውብሸት ታዬ፣ አንዷለም አራጌ፣ ኦልባና ሌሊሳ፣ በቀለ ገርባ፣ አቡባከር እና ሌሎች ብዙዎች በአስቀያሚነቱ በሚታወቀው በመለስ ዜናዊ የቃሊቲ የማጎሪያ እስር ቤት ወስጥ ታስረው በመማቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ምክንያቱም እነዚህ መንፈሰ ጠንካራ ወጣቶች በስልጣን ላይ ያለው ገዥ አካል ትግላቸውን እንዲያቆሙ ቢያስፈራራ እና የማሸበር ድርጊቱን በግልጽ እና በስውር በየጊዜው ቢያካሂድም ለአገራቸው ነጻነት እና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ታጥቀው የተነሱት ወጣቶች ሊበገሩለት አልቻሉም፡፡ እምቢኝ አሻፈርኝ ለነጸነቴ ብለው ቃል በመግባት የጭቆናን አገዛዝ ከስሩ መንግሎ ለመጣል በጽናት ተነስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ በሰላማዊ ትግል ለውጥ ለማምጣት የምናምን ኢትዮጵያውያን/ት በሙሉ የሁሉንም ኢትዮጵያውያን/ት ልብ እና አእምሮ መግዛት ይኖርብናል፡፡ የእኛ ስኬታማነት መለካት ያለበት በጽናት እና ቀጣይነት ባለው መንገድ ህዝቡን አስተምረን በማሳመን በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት በመረጡ ህዝቦች ብዛት ነው፡፡ በስልጣን ላይ ያሉት ኃይሎች ደግሞ ድላቸውን እና ምን ያህል ኃያል እንደሆኑ የሚለኩት በየውጊያ መስኮች ምን ያህል ኢትዮጵያውያን/ት እሬሳዎችን ለመዘረር እንደቻሉ በድንን በመቁጠር ነው፡፡ ይህ የአሁኑ የትግል ውጤት ቀደም ሲል የተተነበየ እና ተግባራዊ የተደረገ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ በአንድ ወቅት ጎልያድ የሚባል በጣም ኃይለኛ የሆነ ሰው ነበር፡፡ የብረት እና የነሀስ ቆብን ለስጋዊ ህይወቱ መሸፈኛ በማድረግ ጎልያድ በተራራው ላይ በመውጣት እብሪት በተቀላቀለበት መልኩ ቀን በቀን ህዝቡን ማስፈራራቱን ቀጠለበት፡፡ በአካባቢው ሁሉም በመፍራቱ ምክንያት ጎልያድን የሚገዳደር አንድም ሰው ጠፋ፡፡ ከዚያም አምላክን ብቻ እንጅ ማንንም የማይፈራ እና ሲያዩት ጥንካሬ የሚጎድለው የሚመስል ዳዊት የሚባል ኮሳሳ ወጣት እረኛ ከመንጋዎቹ መካከል ብቅ አለ፡፡ ዳዊት የወርቅ፣ የብር እና ሌሎች የከበሩ ሽልማቶችን ለማግኘት ሲል የመጣ ሳይሆን የራሱን ወገኖች ኩራት፣ ክብር እና እምነት ለመመለስ በማለም ከጎልያድ ጋር ፍልሚያ ሊያደርግ ወሰነ፡፡ ዳዊት ጎራዴ፣ ጦር፣ መከላከያ ብረት ለበስ ልብስ እና የእራስ የብረት ቆብ ተሰጠው፡፡ ዳዊት  በወንጭፍ እና በ5 ጠጠሮች አማይነት ከጎልያድ ጋር ለመዋጋት መረጠ፡፡ ጎልያድ ባዶ ጩኸት እያሰማ እና በትንሹ ዳዊት ላይ የንቀት ስሜትን በማሳየት ዳዊት ሊገጥመው እንደማይቻለው እየተንጎማለለ ቡራ ከረዩ ማለት ጀመረ፡፡ ዳዊት ጎልያድን አገኘው እና ጎልያድ ምንም ነገር እንዳልሆነ በህሊና ሚዛኑ መዝኖ የተሸከመውን የእብሪት ቀልቀሎ በአንዲት ጠጠር በወንጭፍ ተኳሽነት ማስተንፈስ እንደሚችል በተግባር አረጋገጠ፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በፍርሀት እና በጥላቻ የተሞላው ወያኔ/ኢህአዴግ እየተባለ የሚጠራው ጎልያድን ድል የሚያደርግ የኢትዮጵያ ዳዊት ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ኃቅን እና ኃቅን ብቻ ይዞ የተነሳ ለኃይለኞች ተገዳዳሪ ሆኖ የመጣ የፖለቲካ ፓርቲ ነው፡፡ ወያኔ/ኢህአዴግ የተባለው ጎልያድ ጠብ መንጃዎችን፣ ቦምቦችን፣ ታንኮችን፣ ከባድ መሳሪያዎችን እና የጦር አውሮፕላኖችን ሁሉ አግበስብሶ በመያዝ እስከ አፍንጫው ድረስ ዘመናዊ የጦር ትጥቅ የታጠቀ ሀሰትን የአቅጣጫው መመሪያ ኮምፓስ አድርጎ የተነሳ ቡድን ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በአሁኑ ጊዜ ብዛት ያለው ጨቋኝ የፖሊስ እና የደህንነት ካድሬዎችን ሰብስቦ ከያዘ ከአፍሪካ ተወዳዳሪ ከማይገኝለት ጎልያድ በተጻራሪ የቆመ ፓርቲ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በዓለም አቀፍ ደረጃ በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የገንዘብ እርዳታ እና ብድር ከሚደረግለት እንዲሁም ከህዝብ የተዘረፈ ገንዘብ በማግበስበስ ኃይሉን ካጠናካረ ጎልያድ ጋር ለመገዳደር እና ድል ለማድረግ በተጻራሪ የቆመ ፓርቲ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የጥላቻ እና መለያየት መርዝን ከሚረጨው የጎልያድ ደም፣ ውሸትን እና ማጭበርበርን ከሚፈበርከው የጎልያድ አእምሮ፣ በተስፋ ማጣት እና በመከራ ውስጥ ተዘፍቆ ከሚዳክረው የጎልያድ መንፈስ፣ እና ህይወቱን እና አስትንፋሱን ከሚያጨልመው የጎልያድ ልብ በተጻራሪ የቆመ ዳዊታዊ ጽኑ መንፈስ የተሞላበት ፓርቲ ነው፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ወንጭፍ እንዲሁም ፍቅር፣ እውነት፣ ተስፋ፣ ሰላም እና አንድነት የሚባሉ አምስት ጠጠሮችን ብቻ በመታጠቅ ከወያኔ/ኢህአዴግ ጎልያድ ጋር ለመፋለም ቆርጦ የተነሳ ፓርቲ ነው፡፡ በመጨረሻም ሰማያዊ ፓርቲ በወያኔ/ኢህዴግ ጎልያድ ላይ ድልን ይቀዳጃል፣ እናም ወያኔ ይድናል፣ በእርግጥም ይድናል፣ ምክንያቱም የሰማያዊ ፓርቲ ጠጠሮች ይፈውሳሉ እንጅ አይገድሉም፡፡ ከወያኔ/ኢህአዴግ ጎልያዶች በተጻራሪ ከቆሙት ከሰማያዊ ፓርቲ የኢትዮጵያ ዳዊቶች ጎን ተሰልፌ ለፕሮጀክቱ ግንባታ ስኬታማነት ለህንጻው ጥንካሬ ውኃ ማቀበል በመቻሌ ከፍ ያለ ክብር ይሰማኛል፡፡
ለሰማያዊ ፓርቲ ዕ(ድል) እንስጠው
በተለያዩ የሰማያዊ ፓርቲ የከተማ የስብሰባ አዳራሾች ስብሰባዎች ላይ በመገኘት “ጠቃሚ ንግግሮችን” ሳሰማ በመቆየቴ ልዩ የሆነ ክብር እና ሞገስ ተሰምቶኛል፡፡ እኔ እራሴን “ጠቃሚ ንግግር” አድራጊ አድርጌ አልቆጥርም፡፡ እራሴን የምቆጥረው እንደ አንዳንድ ታሪካዊ የሆኑ ወሳኝ ክንውኖች ሲከናወኑ በማየት ለማስረዳት ፈቃደኛ ሆኖ በመቅረብ “ምስክርነት” መስጠት ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ከወያኔ/ኢህአዴግ ጎልያድ ጋር በሚያደርገው ትግል በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ለሰማያዊ ፓርቲ የውጊያ ዕድል እንዲሰጡ፣ የድጋፍ ዕድል እንዲያደርጉ  ለመጠየቅ እና በተስፋም ለማሳመን ምስክር ሆኘ ቀርቢያለሁ፡፡
ሰማያዊ ፓርቲን በሙሉ ልብ እደግፈዋለሁ፣ ምክንያቱም የኢትዮጵያ ወጣቶች የአገራቸውን ዕጣፈንታ ለመወሰን እና ፍቅር የነገሰባትን አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት ራዕይ፣ ኃይል፣ ብቃት እና ጽናት ያላቸው ብቸኛዎቹ ኃይሎች በመሆናቸው ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት ወደ 94 ሚሊዮን ገደማ እንደሚሆን የሚገመት ሲሆን ከዚህ ውስጥ ዕድሚያቸው ከ35 ዓመት በታች የሚሆነው 70 በመቶውን የሚሸፍነው የወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በብዛት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ሰለባ ሆነው የሚገኙት ወጣቶች ናቸው፡፡ የፖለቲካ ጭቆና እና ማስፈራራት፣ ከህግ አግባብ ውጭ በዘፈቀደ በቁጥጥር ስር የማዋል እና እስራት፣ ማሰቃየት፣ ማዋረድ እና ደካማ የእስር ቤት አያያዝ ሰለባ የሚሆኑት በአብዛኛው በሚባል መልኩ ወጣቶች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ወጣቶች ስር በሰደደ የስራ አጥነት ወጥመድ ተጠፍረው እና የትምህርት እና ኢኮኖሚያዊ ዕድሎችን አጥተው የበይ ተመልካች የሆኑበት ጊዜ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ወጣቶች ለነጻነት እና ለስርዓት ለውጥ የሚያነሱት ጥያቄ በእራሱ ገላጭ ነው፡፡ ለውጥ ሰላማዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ይመጣል ነገር ግን ለውጡ ዘግይቶ እንደሚመጣ ባቡር ነው፡፡ ጥያቄ ሊሆን የሚችለው የኢትዮጵያ ወጣቶች ለውጡ ዕውን እንዲሆን የሚፈልጉት እየጨመረ በመጣው የኃይል አሰላለፍ ነው ወይስ በሰላማዊ መንገድ በሚደረግ ሽግግር ነው የሚለው ነው፡፡
ላለፉት ስምንት ዓመታት በኢትዮጵያ ሲደረግ በቆየው የሰብአዊ መብት ጥበቃ የትግል ሂደት የእራሴን መጠነኛ የሆነች ድርሻ ለማበርከት ሞክሪያለሁ፡፡ ሆኖም ግን ዘግይቸ የወሰድኩት ኃላፊነት ሆኖ ይሰማኛል፡፡ ከእኔ ሳምንታዊ ትችቶቸ እና ንግግሮች ትምህርት አግኝተንበታል በማለት በኢትዮጵያ የአቦሸማኔው እና የአቦ-ጉማሬው ትውልድ ከመስማት የበለጠ ክብር የሚሰጥ ነገር አላገኝም፡፡ መምህር ከዚህ በላይ ምን ሊጠይቅ ይችላል?
ባለፉት ጊዚያት የሰብአዊ መበቶች ጥበቃ ድጋፍ እንድናደርግ እና ለግለሰብ መብቶች ክብር መጠበቅ በሚል እሳቤ ለአንባቢዎች ጥያቄዎችን፣ ልመናዎችን እና ተማጽዕኖዎችን በተደጋጋሚ ሳቀርብ እንደነበር ይታወሳል፡፡ አሁን አንባቢዎቸን የምጠይቀው በእርግጥም የምማጸነው በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያን ህዝብ ፍላጎት ከሁሉም በኢትዮጵያ ውስጥ በመንቀሳቀስ ላይ ከሚገኙት የፖለቲካ ፓርቲዎች የበለጠ ያስጠብቃል የሚል እምነት ለምጥልበት በኢትዮጵያ ወጣቶች ለተገነባው ለሰማያዊ ፓርቲ ድጋፋችሁን እንድታደርጉ ነው፡፡
እኔ ሰማያዊ ፓርቲን ስለደገፍኩት ብቻ አንባቢዎቸ እንዲደግፉት አልፈልግም፣ ሆኖም ግን ለሀገራቸው ራዕይ ባላቸው የአቦሸማኔዎቹ የኢትዮጵያ ወጣቶች የተሞላው የሰማያዊ ፓርቲ ስብስብ እራሱ ለሀገሪቱ ከሚያስገኘው ጠቀሜታ አንጻር ብቻ በአእምሯቸን የፍርድ ሚዛን ተመዝኖ ሊደገፍ ይገባል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲን ለመደገፍ ከውሳኔ ላይ በደረስኩበት ወቅት ጥቂት ጥያቄዎችን አንስቸ ነበር፡፡ እነዚህም 1ኛ) በሰላማዊ መንገድ የማህበራዊ እና የፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት በእውነት ሙሉ እምነት አለኝን? 2ኛ) በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት ሙሉ እምነት አለኝ ካልኩ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ካለው ነባራዊ ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር የትኛው የፖለቲካ ፓርቲ ነው ይህንን ዓላማ በተሻለ እና ውጤታማ በሆነ መልኩ ወደ ተግባር ሊቀይረው የሚችል? 3ኛ) እንደዚህ ያለውን ለውጥ የኢትዮጵያ ወጣቶች የፈጽሙታል የሚል እምነት ካለኝ እነርሱን ለማገዝ ምን ማድረግ እችላለሁ?
በውጭ የምንገኝ የዲያስፖራው ማህበረሰብ አባላት በሙሉ ሰማያዊ ፓርቲን በተለያዩ መንገዶች ልንደግፈው እንችላለን፡፡ አቅሙ ያላቸው የተቻላቸውን ያህል በገንዘብ ሊደግፉ ይችላሉ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ድርጅታዊ ስራውን በተቀላጠፈ መልክ ለመስራት እና ብዙሀኑን የወጣት ክፍል ለመድረስ ለሚያድርጋቸው ጥረቶች ብዙ ገንዘብ ይፈልጋል፡፡ ሌሎችም ከእዚህ ያላነሱ ለሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ልናደርግባቸው የምንችልባቸው መንገዶች አሉ፡፡ ስለሰማያዊ ፓርቲ ማወቅ እና ሌሎችን ማስተማር ታላቅ ጠቀሜታ ያላቸው ድጋፎች ናቸው፡፡ ለሰማያዊ ፓርቲ በሁሉም መስኮች ያተኮረ የፖሊሲ ትንተና እና ልማትን ያካተተ የቴክኒክ ድጋፍ ማድረግ ጠቀሜታው የጎላ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ምሁራን እና የአካዳሚው ማህበረሰብ በዚህ ረገድ ወሳኝ ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲን የተስፋ፣ የአንድነት እና የሰላም መልዕክቶች ለሌሎች መረጃው ለሌላቸው ወገኖቻችን ማሰራጨት ከሌሎች ድጋፎች ሁሉ የበለጠ ጠቃሚ ድጋፍ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲን ከሚሰነዘሩበት የውሸት ውንጀላዎች እና ክሶች እንዲሁም የፍርሀት እና ጥላሸት የመቀባት ዘመቻዎች መከላከል ጠቃሚ ድጋፍ ነው፡፡ የሞራል ድጋፍ መስጠት እና ለሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች እና አባላት ከፍተኛ የሆነ የማበረታቻ ድጋፍ ማድረግ ሌላው ታላቅ ድጋፍ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲን ማድነቅ ማንም ኢትዮጵያዊ/ት ጀግና አርበኛ ሊያደርገው/ልታደርገው የሚገባ ታላቅ ድጋፍ ነው፡፡
የግል ምልከታ
ከሰማያዊ ፓርቲ የድጋፍ ስብስብ ወጣቶች ጋር መስራት ለእኔ የሚያስደንቅ ልምድ ነው፡፡ ለበርካታ ዓመታት በሳምንታዊ ትችቶቸ እና አልፎ አልፎ በማደርጋቸው ንግግሮች የኢትዮጵያ ወጣቶችን ለማስተማር፣ ለማሳወቅ እና ብዙሀኑን ወጣቶች ለመድረስ የተቻለኝን ያህል ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲጠናከር እና ከፍ ወዳለ ምዕራፍ እንዲሸጋገር ጥረት ሲያደርጉ ለቆዩት እና አሁንም በማድረግ ላሉት ወጣት ፕሮፌሽናሎች፣ የንግድ የስራ ፈጣሪዎች/ኢንተርፕሪነሮች እና የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በአማካሪነት ደረጃ ተመድቤ እያገለገልኩ በመሆኔ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የሰማያዊ ፓርቲ የድጋፍ ስብስቦች በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተጠናከሩ መምጣት የኢትዮጵያ የአቦሸማኔ ወጣቶች ተባበሩ በፍጹም እጅ እንዳትሰጡ የሚለውን እምነቴን የበለጠ እንዲቀጣጠል አድርጎታል፡፡
ስለሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ስለይልቃል ጌትነት ያሉኝን የእራሴን ጥቂት ምልከታዎች ላካፍላችሁ፡፡ ባለፉት ስምንት ዓመታት ከበርካታ የኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ የንግድ እና የማህበረሰብ መሪዎች ጋር በአንድ ወይም በሌላ መልኩ ተገናኝቻለሁ፡፡ ብዙዎቹ እነዚህ መሪዎች የሚያስደምሙ ስብዕናዎች አሏቸው፡፡ ለማንኛውም የፖለቲካ መሪ ባህሪ ዋና የስብዕና ማረጋገጫ ነው የሚል አመለካከት አለኝ፡፡
ይልቃል የፕሮፌሽናል እና የቤተሰቡን ፍላጎት በመግታት ለኢትዮጵያውያን/ት ወገኖቹ ነጻነት በማለም በኢትዮጵያ ሰላማዊ የለውጥ ሽግግር ለማድረግ ሌት ከቀን የሚታትር ወጣት መሀንዲስ ነው፡፡ እንዲህ አይነቱን ምርጫ ለመወሰን ታላቅ ስብዕናን እና ግላዊ የመንፈስ ጥንካሬን ይጠይቃል፡፡ በጉብኝት ጊዚያችን የይልቃልን ዘርፈብዙ ባህሪያት ለመመልከት ችያለሁ፡፡ የመርህ ሰው መሆኑን በተግባር አስመስክሯል፡፡ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት በሚል እየተከተለ ያለው ምዕናባዊ ሀሳብ እንጅ አሁን ካለው የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ አኳያ በተግባር ሊውል እንደማይችል እና ይህ አካሄድ ከውድቀት እንደማያድን የሚፈታተኑ ጥያቄዎች ቀርበውለታል፡፡ እርሱም የክርክር ጭብጦቹን በሚያሳምን መልኩ አዘጋጅቶ ኃይል የደካሞች መሳሪያ መሆኑን፣ ማንም ቢሆን በጉልበት እና በኃይል ተጠቅሞ ልብን እና አእምሮን ሊቀይር እንደማይችል አጽንኦ በመስጠት ለማሳመን ጥረት አድርጓል፡፡ ኢትዮጵያ የክልሊስታንስ (የክልሎች) አወቃቀር እንደያዘች መቀጠል ያለባት ትክክለኛ የፖለቲካ መስመር መሆኑ ታምኖበት መስተካከል ያለበት ነገር ቢኖር “የብሄሮችን እና የብሄረሰቦችን” መብት ከማስከበር ላይ ነው የሚል ሌላ ፈታኝ አስተያየት ቀርቦለት ምላሽ ሰጥቷል፡፡ የግለሰብ መብቶች ሲከበሩ እና ጥበቃ ሲደረግላቸው የቡድን መብቶችም በዚያው ልክ ይከበራሉ ጥበቃም ይደረግላቸዋል የሚለውን መርህ በማንሳት በሚያሳምን ሁኔታ ለማብራራት ሞክሯል፡፡ በሌላም በኩል መብት ደፍጣጩ ገዥ አካል እርሱን እና ሌሎችን በሰማያዊ ፓርቲ አመራር ላይ ያሉትን ሰዎች መብት ቢደፈጥጥ፣ ቢያስር፣ ቢያሰቃይ እና ቢገድል ምን ዋስትና አለ የሚል ሌላ ፈታኝ አስተያየት ቀርቦለት ነበር፡፡ እርሱም ሲመልስ ይህ ይፈጸማል በሚል እንደማይፈራ ምክንያቱም እርሱና ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ የአመራር አባላት ይህንን ፓርቲ ገና ከመጀመሪያው አልመው ሲመሰርቱ ትክክለኛውን ነገር ለመስራት ለአገራቸው እና ለወገኖቻቸው ነጻነት ሲባል ማንኛውንም መስዕዋትነት ለመክፈል ዝግጁነታቸውን አረጋግጠው እንደሆነ በማስገንዘብ በሙሉ ልብነት ይህ አያስፈራንም ብሏል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በወጣቱ እና በቀድሞው ትውልድ መካከል የልዩነት መስመር በማስቀመጥ ልዩነትን ሲያራምድ የቆየ ነው በሚል ትንተና እና ጩኸት የቀረበለትን ሀሳብ ይህ የሀሰት ውንጀላ ነው በማለት አስተባብሏል፡፡ እንደ መርህ ስንወስደው በትውልዶች መካከል የስራ ክፍፍል መኖር አለበት በማለት ጉዳዩን ግልጽ አድርጎታል፡፡ የኢትዮጵያ የቀድሞው ትውልድ አባላት አማካሪዎች እና ድጋፍ ሰጭዎች በመሆን ወሳኝ ሚና መጫወት ያለባቸው ሲሆን ወጣቱ ትውልድ ደግሞ ከባዱን ሸክም ለማንሳት በየመንገዶች መደብደብ እና እየተያዘ በእስር ቤቶች ታስሮ እየማቀቀ ለነጻነት የሚደረገውን ትግል ዓላማ ከግብ ማድረስ ይሆናል፡፡ ሆኖም ግን የመጨረሻውን ወሳኙን ለውጥ ለማምጣት ፍላጎቱ፣ ጽናቱ፣ ብቃቱ፣ ኃይሉ እና የፈጠራ ችሎታው ያለው በኢትዮጵያ የአቦሸማኔ ወጣቶች ትከሻ ላይ ነው ብሏል፡፡ “አሜን!” ብያለሁ፡፡ ይልቃል የእርሱ ፓርቲ ከሌሎች የገዥውን አካል ከሚቃወሙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር “ህብረት” በመፍጠር ለመታገል ጥረት  ለምን እንደማያደርግ ከባድ ወቀሳ ተሰንዝሮበታል፡፡ በምላሹም የእርሱ ፓርቲ ከሌሎች የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር አብሮ እየሰራ እና እያስተባበረ እንዳለ ሆኖም ግን ከሌሎች የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር መሰረታዊ የሆኑ የፖሊሲዎች፣ የእስትራቴጂዎች እና የስልቶች ልዩነቶች ስላሉ “ህብረት” የመፍጠር እንቅስቃሴውን ፈታኝ ያደርገዋል ብሏል፡፡ አያይዞም በውጭ የምንገኘው የዲያስፖራ አባላት በአገር ውሰጥ ያሉትን የተቃዋሚ ኃይሎች ለምን ህብረት ፈጥረው በአንድነት አይታገሉም በማለት በተደጋጋሚ በመተቸት ከመውቀስ ባለፈ በውጭ የምንገኘው የዲያስፖራው ማህበረሰብ አባላት እራሳችን ህብረት በመፍጠር በአንድነት በመስራት በኢትዮጵያ ተንሰራፍቶ የሚገኘውን አምባገነንነት በመታገል ለሌሎች በሀገር ቤት ላሉት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አርዓያ ሆናችሁ አታሳዩም በማለት ጥያቄውን በጥያቄ በመመለስ ይህ ጉዳይ ሁልጊዜ የሚገርመው መሆኑን ገልጿል፡፡
ይልቃል ትንሽ ተክለሰውነት ያለው ወጣት ነው፡፡ በቀረቡለት ከአንድ በላይ የሆኑ ቀጥተኛ ፈታኝ ጥያቄዎች ሁሉ በሰለጠነ መንገድ ተገቢውን መልስ እና አስተያየት ሰጥቷል፡፡ በእውነት ለመናገር ይልቃል እውነተኛ ስልጡን አንጋፋ መሆኑን በተግባር አስመስክሯል፡፡ በየሄደበት ቦታ ላገኛቸው ወገኖቹ ሁሉ ቅንነት እና አድናቆት የተሞላበት አቀራረብን አሳይቷል፡፡ በየደረሰበት ሊያናግሩት የሚሞክሩትን ወገኖች ሁሉ በጥሞና እና በትዕግስት ሲያዳምጣቸው ነበር፡፡ ሆን ተብሎ ስሜትን የሚፈታተኑ ጥያቄዎች በቀረቡለት ጊዜም በተረጋጋ እና ከስሜታዊነት በጸዳ መልኩ ምላሾችን ሲሰጥ ነበር፡፡ ወደ እውነታው ለመድረስ በሚደረገው ግንኙነት ሁሉ ያለምንም ስሜታዊነት በትዕግስት ከማዳመጥ እና ከመመለስ በስተቀር ተቃራኒውን ሲያሳይ አልተስተዋለም፡፡ እራሱን “የፓርቲ መሪ” ወይም ደግሞ ልዩ የሆነ ሰው አድርጎ አላቀረበም፡፡ በቀላሉ ሊገኝ የሚችል እና በህዝብ እና በግል ጉዳዮቹ በሚደረጉት ግንኙነቶች ሁሉ ቀናነት እና ግልጽነትን ሲያሳይ ነበር፡፡
የይልቃልን ስብዕና አድንቂያለሁ፡፡ ብዙዎችን ቦታዎች ስንጎበኝ በነበረበት ጊዜ የአቦሸማኔው እና የጉማሬው ትውልድ በየከተሞቹ የስብሰባ አዳራሾች ሁሉ ጢም ብሎ እስኪሞላ እናገኛቸዋለን በማለት ላሳምነው ሞክሬ ነበር፡፡ ከመድረኩ ጀምሮ እስከ ታዳሚው መቀመጫ ድረስ ከእያንዳንዱ የጉማሬው (የቀድሞው ትውልድ) አባላት ጎን የአቦሸማኔው (የወጣቱ ትውልድ) ተቀምጦ ይመለከት ነበር፡፡ የትኞቹ የአቦሸማኔዎች እና የትኞቹ ደግሞ የጉማሬው ትውልድ አባላት እንደሆኑ እንዳመለክተው ጠየቀኝ፡፡ በፍጹም መለየት አልቻልኩም፡፡ የቀድሞው ትውልድ አቦሸማኔዎች ከወጣቱ ትውልድ አቦሸማኔዎች አጠገብ ተቀምጠው ይታዩ ነበር፡፡ በጣም ጠቃሚ ትምህርት ተምሪያለሁ፡፡ የወጣቱ ወይም የቀድሞው ትውልድ መሆን ማለት የአዕምሮን ሁኔታ እንደ የአእምሮው ባለቤት ስብዕና ሁኔታ የማመሳል ያህል ነው፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ አቦሸማኔ ትውልዶችን ለመደገፍ በመውጣት በየስብሰባ አዳራሾች ሁሉ ለተገኛችሁ የወጣቱና እና የቀድሞው ትውልድ አቦሸማኔዎች ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋናየን አቀርባለሁ!

አንባ ገነኑን የወያኔን መንግስት በቃ ልንለው ይገባል (ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ )


 
 
ማብቄያ የሌለው የወያኔ አረመናዌ ድርጊት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመጣበት በዚህ ጊዜ ሰሞኑን ለእራሴ አንድ ጥያቄ ጠየቁትኝ እስከመቼ ነው የወያኔ መቀለጃ እና መጫወቻ ሆነን የምንኖረው እስከመቼ ነው ወያኔ ህዝባችንን እያሰቃየ እና እየጨቆነ የሚኖረው እስከመቼ ነው ዜጓች መብታቸው ታፍኖና ነጻነታቸው ተረግጦ በሃገራቸው መብታቸው ሳይከበር እንደ ዜጋ ሳይሆን እንደ ሁለተኛ ዜጋ እየተቋጠሩ የሚኖሮት እኔ እንደማስበው በአሁኑ ጊዜ ሀገራችንን እየመራ ያለው የወያኔ መንግስት  ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውነትን ሊያጠፋ የተነሳ መንግስት ይመስለኛል ግን እስከ መቼ ነው የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት በዚህ ርኩስ ባህሪውና ድርጊቱ የሚቀጥለው ? በቃልንለው ይገባል::
መቼም ይህ ጥያቄ የሁላችንም ሀገር ወዳድ እና ነጻነት ናፋቂ ኢትዮጵያኖች ጥያቄ ይሆናል ብዬ አስባለው እስከመቼ _?
 እኛ ኢትዮጵያኖች መብታችን ተረግጦ  ነጻነታችን ተገፎ በዲሞክራሲ ቸነፈር ተመተን መኖር ከጀመርን ይኸው ከድፍን ሁለት አስር አመታቶች በላይ አስቆጠርን በእነዚህ  ዓመታቶች ብዙዎች ለዲሞክራሲ፤ ለፍትህና ለነፃነት ታግለዋል አሁንም ቡዙዎች በሚችሉት መንገድ ሁሉ ይኼ ዘረኛውን እና አንባ ገነኑን የወያኔን መንግስት እየተፋለሙት ይገኛሉ::ነገር ግን ለዲሞክራሲ፤ ለፍትህና ለነፃነት የታገሉ ብዙዎች  በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ  ዜጎች አልቀዋል፤ ለስደትም ተዳርገው ለብዙ መከራ ሰለባ ሆነዋል፡፡ ቁጥራቸው እጅግ ብዙ የሆነ የሀገሪቷ ዜጓች ደግሞ በአሁኑ ሰዓት በሀገሪቱ በሚገኙ እስር ቤቶች ታስረው በወያኔ ካድሬዎች ጭካኔ የተሞላበት ኢ ሰበአዊ ድርጊት እየተፈጸመባቸው በሰቃይ እና በመከራ ውስጥ ሲገኙ አንዳንዶቹም በሚደርስባቸው ስቃይ እና በወያኔ መጥፎ ሴራ እዛው ወህኒ ቤት ውስጥ እይውታቸው እያለፈ ይገኛል:: ለዚህ ማሰረጃ የሚሆነን  በቅርቡ ከጅጅጋ 25 ኪሜ ገደማ እርቃ በምትገኘው ቀብሪበያህ እስር ቤት ውስጥ የሞቱት ከ40 በላይ የሚሆኑ ንጹሃን ኢትዮጵያ ዜጓቻችን ምስክር ነው:: አረ ስንቱ ይዘረዘራል የወያኔ መንግስት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለው በደል ቢዘረዘር ማለቂያ የለውም :: ወያኔ በስልጣን በቆየባቸው በእነዚህ አመታቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ ነገሮች መሻሻል እና መስተካከል ሲገባቸው ነገሮች ሁሉ በተገላቢጦሽ  እስራቱ፣ግድያው፣ስደቱ፣ድህነቱ ፣ ሁሉ ነገር እየባሰ እና ከጊዜ ወደ ጊዚ እየጨመረ መምጣቱ ሀገራችን ኢትዮጵያ በጣም አሳሳቤና አስጌ  ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ አመልካች ነገር ነው::
 
ወያኔዎች እኔ ከሞትኩኝ ሰርዶ አይብቀል እንደሚባለው  የሀገሬቱን ሀብት እየዘረፉ እና እየቦጠቦጦ እንዳሻቸው መኖርን አልበቃም ብሏቸው ቅንጣትም ያክል ስለ ኢትዮጵያም ቢሆን ስለ ኢትዮጵያዊነት ግድ እንደሌላቸው በሚያሳይ መንገድ  በማን አለብኝነትና በግድ የለሽነት  ለግል እና ለእራሳቸው የፖለቲካ ጥቅም ቀደምት አባቶቻችን ለሀገራችን ዳር ድንበር መስዋዕት የሆኑለትን እና ደማቸውን ያፈሰሱለትን መሬታችንን ድንበራችንን እንኮን ሳይቀር ለባህድ አገራት በመስጠት ላይ እንዳሉ ሲሰማ ማንንም ኢትዮጵያዊ የሆነ ዜጋ ሁሉ የሚያስቆጣ እና የሚያንገበግብ ነው ብዬ አስባለው:: በጣም የሚገርመው እና የሚያሳዝነው ነገር ወያኔዎች  የገዛ ወገኖቻችንን የሀገሪቱን ዜጓች ሀብት እና ንብረት ካፈሩበት ሀገርና መሬት ላይ ሀብትና ንብረታቸውን እየዘረፉና ቤታቸውን እየፈረሱ ከሚኖሩበት ቄዬ እያባረሩ ለውጭ አገር ሰዎች ደግሞ የሀገሬቷን መሬት እየቸበቸቡ መኖርን የለመዱበት ተግባራቸው መሆኑ ነው :: 
እያደር ብዙ ይሰማል እንደሚባለው የወያኔን መንግስት  አሁንም ዝም ካልነው ሌላ ብዙ አስርት የመከራ አመታትን መጋፈጥ ሊኖርብን ነው፡፡ እስከመቼ ዝም እንደ ምንለው ግን ወገን አይገባኝም ፡፡ ወያኔ እያደረገው ስላለው አረመናዊ ድርጊቶ ፋታ ልንሰጠው አይገባም ::  አሁንም ህፃን፤ ወጣት፤  ጐልምሳና አዛውንት ወገኖቻችን ሲረግፍ፤ ሲሰደዱ ፣ የኢትዮጵያ ገጽታ ሲበላሽና ፣ በደምና በአጥንት መስዋዕትነት ተከብሮ የቆየውን የሃገራችንን ዳር ድንበር የወያኔ መንግስት ለባዕድ አሳልፎ ሲሰጥ ማየት ከሆነ ህልማችን መልካም! ግን ይህንን የሚያልምም ሆነ የሚመኝ ንፁህ ኢትዮጵያዊ ያለ አይመስለኝም፤ ከራሳቸው ከወያኔ ሆድደር ካድሬዎች በስተቀር፡፡ ስለዚህ ወገኔ ሆይ ይህንን መንግስት ዝም ብለን ልናየው አይገባም፡፡ ወይም እንደ ፈለገ ሊፈነጭብን ቦታ መስጠት የለብንም፡፡ እስካሁን በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያደረሰው ጭቆናና በደል እንዲያውም በምን አለብኝነት የኢትዮጵያን ቅርጽ እና ታሪክ የሚያበላሸውን የወያኔ እንቅስቃሴ  ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጋ ዘር፣ ጎሳና ፆታ ሳይለይ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውነትን እያጠፋ ባለው በወያኔ መንግስት ላይ ሆ ብለን በአንድነት በመነሳትና በመጮህ ይበቃል ልንለው እና ልናስቆመው  የግድ ነው፡፡ 
 
በቃ በቃ በቃ !!!
 
      ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኖራለች!!!

ከቃሊቲና ቂሊንጦ እስር ቤቶች በላይ የሚያንጸባርቁ ከዋክብት (ዳዊት ከበደ ወየሳ፣ አትላንታ)


ዳዊት ከበደ ወየሳ (አትላንታ)
(ይህ ጽሁፍ የርዕዮት አለሙ የልደት በአል በአዲስ አበባ በተከበረበት ወቅት; ከውጭ አገር ንግግር እንዳደርግ በተጋበዝኩበት ወቅት… የስራ ባልደረቦቼን እስክንድር, ውብሸት እና ርዕዮትን በማሰብ የተዘጋጀ ነው)
ይህ ሳምንት የታላቁ ማርቲን ሉተር ኪንግ የልደት በአል በመላ አሜሪካ የሚከበርበት ነው:: በአሜሪካ ከክርስቶስ ልደት ቀጥሎ ስራ እና ትምህርት ቤት ተዘግቶ ልደቱ የሚከበርለት አንድ ሰው ቢኖር ማርቲን ሉተር ኪንግ ብቻ መሆኑን ልብ ይበሉ:: የማርቲን ሉተር ኪንግ የልደት በአል በሚከበርበት ወቅት በህይወት ዘመኑ ለጥቁር ህዝብ ነጻነት ያደረገው አስተዋፅኦ ይታወሳል:: በህይወት በነበረበት ወቅት ለሰው ልጅ እኩልነት ተሟግቷል; የነጻነት ቀንዲልን ለኩሷል:: ሆኖም እኩልነት እና ነጻነትን ሳያጣጥም በበርሚንግሃም እስር ቤት ተጥሎ ፍዳውን እንዲቆጥር ተፈርዶበት ነበር:: በመጨረሻም የሰውን ልጅ ክብር እና ነጻነት በማይደግፉ ሰዎች ህይወቱ ማለፉ ይታወቃል – መልካም ስራዎቹ ግን አላለፉም::Reeyot Alemu, the 31 year-2012 Courage in Journalism Award winner.
ዛሬም በአገራችን ስለፍትህ, ስለነጻነት የሰበኩና የደሰኮሩ; የጻፉና የመሰከሩ… ለሃቅ ቆመው፣ ግፍ የተሰራባቸው፣ ከአገር የተሰደዱና የወጡ፤ በግፍ ሰንሰለት ለጨለማ እስር የተዳረጉ ወገኖቻችን ብዙ ናቸው:: እስክንድር፣ ውብሸት፣ ርእዮት፣ አንዷለም እና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ራሳቸውን በሰብአዊነት መሰረት ላይ ስላነጹ እና ሃሳባቸውን በነጻነት ስለገለጹ መጨረሻቸው እስር እና እንግልት ሆኗል::
እንደ እውነቱ ከሆነ ሃሳብን በነጻነት መግለጽ… ብሎም የህዝብ ልሳን ሆኖ ለህዝብ የቤዛነት ዋጋ መክፈል የሚያስከብር እንጂ የሚያሳስር አልነበረም:: በመሆኑም ለነጻ ፕሬስ መክፈል የሚገባቸውን ዋጋ ከመጠን አሳልፈው የከፈሉት፤ ርዕዮት አለሙ፣ እስክንድር ነጋ እና ውብሸት ታዬ… ሶስቱም ከአገራቸው አልፈው በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝተዋል:: በአለም አቀፍ ደረጃም በልዩ ልዩ አለም አቀፍ የጋዜጠኞች ማህበራትና ተቅውውማት ለሽልማት ታጭተው አሸናፊ ሆነዋል::
የ’ነዚህ የስራ ባልደረቦቼ ብዕር… ህዝብን ሳይሆን የተወሰኑ ወገኖችን አሸብሮ ሊሆን ይችላል:: እነርዕዮት አለሙ በዚህ አይነት ሰበብ አስባብ በቃሊቲ እና በቂሊንጦ እስር ቤት ታግተው፤ ነጻነታቸውን አጥተውና ህክምና ተነፍገው ይታሰሩ እንጂ፤  ለእውነት የቆሙ ወገኖች ግን ለመልካም ስራቸው ሽልማትን አልነፈጓቸውም::
ማርቲን ሉተር ኪንግ በበርሚንግሃም እስር ቤት ታስሮ ቢማቅቅም የአሜሪካም ሆነ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ አልዘነጋውም:: ቆይቶም ቢሆን የአለም አቀፉ ኖቤል ተሸላሚ እስከመሆን ደርሷል:: ዛሬ በእስር ላይ የሚገኙት የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች የኖቤል ተሸላሚ ባይሆኑም አለም ግን አልረሳቸውም:: ከታሰሩበት የጨለማ ወህኒ ቤት ጀርባ፤ ከብረት ፍርግርግ እና ከግድግዳዎቹ ባሻገር በመቶዎች፣ በሺዎች እና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች እነዚህን ጋዜጠኞች በመልካም ስራቸው ያስታውሷቸዋል; ይዘክሯቸዋል:: ስለሆነም የጻድቃን ሞት፤ የሰማዕትነት ጽድቅ ተደርጎ እንደሚቆጠረው ሁሉ… የነ እስክንድር፣ ውብሸትና ርዕዮት እስር፤ ከቶውኑ ዋጋ ቢስ እና ፍሬ አልባ ሊሆን አይችልም::
ኢትዮጵያ ውስጥ በነበርኩበት ወቅት በፕሬስ ጉዳይ ተደጋጋሚ የሆነ እስር ደርሶብኛል:: በ’ነዚህ የእስር እና እንግልት ጊዜያት ግን… ከጨለማው እስር ቤት ማዶ ለምን እንደታሰርኩ የሚረዱ ሺዎች በመኖራቸው ሁልጊዜ እጽናና ነበር:: በተደጋጋሚ እስር ቤት እየመጣ የሚጠይቀኝ እና የዋስ መብቴን አስጠብቆ ከእስር እንድወጣ ያደርገኝ የነበረው ወላጅ አባቴ፤ “የታሰርከው ሰርቀህ ወይም ሌላ ወንጀል ሰርተህ ሳይሆን፤ እውነትን ስለተናገርክ ነው:: ስለዚህ አንገትህን ቀና ልታደርግ እንጂ ልትሸማቀቅ አይገባህም::” የሚል አጽናኝ ቃል ሁሌ ይነግረኝ ነበር:: ዛሬ አባቴ በህይወት የለም:: ቃሉ እና ምክሩ ግን አብሮኝ አለ:: በእስር ላይ ለሚገኙ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች፤ “አንገታችሁን ቀና አድርጉ!” የሚለውን መልዕክት አጋራቸዋለሁ::
ዛሬ በጋዜጠኞቻችን ላይ የተለያዩ ክሶች ተመስርቶባቸው መታሰራቸው ሳያንስ; ከታሰሩም በኋላ በሃሰት ሊወነጅሏቸው የሚሹ ብዙ ግራ ዘመም ሰዎች መኖራቸውን ታዝበናል:: በአሜሪካ ከፍተኛ የአየር ሽፋን አግኝቶ ዲሞክራቶችን በመሳደብ የሚታወቀው ራሽ ሊምቦ የተባለ ጋዜጠኛ በቅርቡ ኔልሰን ማንዴላ በሞት ሲለዩ… “ብታምኑም ባታምኑም ኔልሰን ማንዴላ አሸባሪ ነበሩ::” ብሎ ሰፊ ሙግት ፈጥሮ ነበር:: ይህ አባባሉ ለኛ እና ለሌሎች አፍሪቃውያን ሊገርመን ይችል ይሆናል:: ነገር ግን የራሳቸው አመዛዛኝ ህሊና ያልፈጠረባቸውና ይህን ሰው በጭፍን የሚከተሉት ሰዎች “አዎ ማንዴላ አሸባሪ ነበሩ” ብለው ቢሉ ሊገርመን አይገባም::
ዛሬም ባገራችን በተመሳሳይ መልኩ የነርዕዮት አለሙን መልካም ስም ጥላሸት ለመቀባት እላይ ታች የሚሉ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ… እኛ ግን እንላለን:: “ወንጀል አልሰራችሁምና አንገታችሁን ቀና አድርጉ!” ስማችሁ ከቃሊቲና ከቂሊንጦ እስር ቤቶች በላይ፤ በጠራው ሰማይ ላይ ያንጸባርቃል፤ ቃለ ሃቃቹህ በአየር ናኝቶ… ኢትዮጵያዊያን ባሉበት ሁሉ በመላው አለም ላይ ተሰራጭቷል::
የማርቲን ሉተር ኪንግ ልደት ሲከበር መልካም ስራዎቹ እንደሚወደሱ ሁሉ፤ ዛሬም ሆነ ወደፊት የነርእዮት አለሙ ልደት ሲከበር መልካም ስራዎቻቸው በተደጋጋሚ ይነሳሉ ይዘከራሉ:: ዛሬ ማንዴላን አሸባሪ ብለው የሚከሱ ሰዎች እንደመኖራቸው መጠን; በተመሳሳይ መልኩ ለነርእዮት አለሙ ተመሳሳይ ስም የሰጡና ያሰጡ… ለመስጠት እና ለማሰጠት የሚጥሩ ሰዎች አሉ:: እኛ ግን የተለኮሱ ሻማዎች ይዘን ልደት ስናከብር; የብርሃናችን  ጮራ፤ ሌሎች የፈጠሩትን የጨለማ ድባብ ሰንጥቆ… አንዳች ብርሃን እንደሚፈነጥቅላቸው በማመን ነው:: ዛሬ የርዕዮት አለሙን የልደት ቀን ስናከብር፤ ያለፍትህ የታሰሩትን ፍትህ የሚፈልጉትን፤ ነጻነት የተጠሙትን ነፍሶች በማሰብ ጭምር ነው::
መልካም ልደት – ርዕዮት!

Ethiopia Has a Terrible Human Rights Record – Why Is the West Still Turning a Blind Eye?

2014-01-23-IMG_0008.JPG
Eleanor Ross

Writer and journalist based in London
Some disappeared, others were given lengthy prison sentences. One thing all thirty men arrested in 2012 in Ethiopia had in common was that they had criticised the state and the policies of the former Premier, Meles Zenawi.
And yet last week Japan’s Prime Minister Shinzo Abe and a group of Japanese business leaders met with the current Prime Minister of Ethiopia, Hailemariam Desalegn to discuss further support for Ethiopia at “government and private sector level.”
The former Meles Zenawi was a staunch supporter of American counter-terrorism policy while at the same time overseeing a country with a violent human rights record. In the eyes of the USA, Ethiopia is strategically situated. Located in the Horn of Africa, next to Somalia, northern Kenya and Sudan, it acts as a buffer zone between the growing Islamic extremism of Somalia and the West. As a result, the human rights violations of Zenawi were ignored.
As one of the first signatories of the UN in 1948, Ethiopia is a Western ally: 11 per cent of its entire GDP comes from Foreign Aid. The US is one of Ethiopia’s largest donors: it is estimated that it gave $3.3bn in 2008 alone. The two countries benefited from their close relation: there have been rumours that America hosted “black sites” in Ethiopia; bases where the CIA interrogated undeclared prisoners during the “War on Terror.”
But Meles Zenawi died in 2012. The opportunity for a more liberal government was not seized: Zenawi was replaced by Hailemariam Desalegn, described by critics as an “identikit Zenawi” running the country on “auto-pilot”. Desalegn is following the same political manifesto as Meles – he hasn’t changed one member of parliament.
The arena for debate and discussion is narrowing. Critics argue that Ethiopia is fast becoming a “one party democracy” where there are many parties but the same one wins again and again. Meles spoke to foreign press in 2005 and defended his 97 per cent electoral victory: “In democracies the party with the best track record remains in power.” The years since 2005 have seen growing unrest among the Ethiopian population and serious repression against critics of the regime. Human Rights Watch reported that Ethiopia “continues to severely restrict freedom of movement and expression”. It adds that “30 journalists and opposition members have been convicted under…vague anti-terrorism laws”.
The day before World Press Freedom Day on May 2 2013, the Ethiopian government ruled to uphold the imprisonment of one of its most well-known prisoners of conscience, Eskinder Nega. He was jailed for being a journalist who criticised the government, and yet, by standing up for his beliefs and expressing his basic human right for Freedom of Speech, he earned an 18 year jail sentence.
Prime Minister Hailemariam Desalegn has denied his release. America and Britain have done little to challenge their ally, so worried are they about creating another enemy in the Horn of Africa. Britain and America have consistently failed to challenge their ally about its abhorrent Human Rights record. Ethiopia flaunts its apathy towards the UN convention of Human Rights, denying opposition members a right to fair trial and repressing people for trying to voice their opinions peacefully.
Ethiopian political repression is worsening. There have been repeated crackdowns against the country’s Muslim minority. This has included arbitrary arrests as Muslims make peaceful demands for freedom of worship. Again, critics have voiced concern with the regime. Mehari Taddele Maru, head of the African Conflict Prevention Program at the Institute for Security Studies expressed concern that “if legitimate grievances are not met then there is a risk that extremist violent elements will exploit those grievances to further their own.”
The world is waking up to Ethiopia’s increasingly poor human rights track record and yet the United States hasn’t stopped aid flowing to Ethiopia or threatened the country with sanctions. Japan still tries to conduct business with Ethiopia when instead they should be holding Ethiopia to account.
As a founding member of the UN and an “ally” of the West, Ethiopia must be held accountable for her crimes. If the West does not challenge Ethiopia and demand that it releases its prisoners who have been locked up without fair trial, then notions of democracy and human rights accountability as embedded in the Human Rights Charter look ever more vulnerable-Human Rights globally will be laughed out of the door.

የወያኔ የውሸት ዘገባዎች ሲጋለጡ

26351fb59e29fb0a1375427042
“ኦክስፋም” በመልካም ሥራቸው ከታወቁ ትላልቅ ዓለም ዓቀፍ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አንዱ ነው። በቅርቡ አንድ መቶ ሀያ አምስት አገሮችን ያካተተ ከምግብ አቅርቦትና አጠቃቀም ጋር የተያያዘ ጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል። ጥናቱ አራት ዝርዝርና አንድ አጠቃላይ አመላካቾች አሉት።
1. አመላካች አንድ: የምግብ እጥረት
ይህ አመላካች “በየአገሮቹ ምን ያህል ለበላተኛው የሚበቃ ምግብ አለ?” የሚለውን ይለካል። በጥናቱ ውጤት መሠረት በምግብ እጥረት እጅግ የተጎዱ የመጨረሻዎቹ አስር አገሮች የሚከተሉት ናቸው: – ቡሩንዲ፣ የመን፣ ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ ናይጄሪያ፣ ላኦስ፣ ባንግላዴሽ፣ መካከለኛዉ አፍሪካ ሪፑብሊክ እና ህንድ። ኢትዮጵያ አገራችን ከመጨረሻ አራተኛ ናት።
2. አመላካች ሁለት: ለምግብ የመክፈል አቅም (Affordability)
ይህ አመላካች “የአገሩ ሕዝብ በአገሩ ዋጋ ምግብ ገዝቶ ለመብላት ምን ያህል አቅሙ ይፈቅድለታል?” የሚለውን የሚመልስ ነው። አሁንም ከመጨረሻ እንጀምር። አንጎላ፣ ዚምባቡዌ፣ ቻድ፣ ጉያና፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ ኮንጎ፣ ኬንያ፣ ጋምቢያ እና ኢራን የየአገሩ ሕዝብ ምግብ መሸመት የሚቸገሩባቸው አገሮች ናቸው። አገራችን ኢትዮጵያ ከመጨረሻ አምስተኛ ናት።
3. አመላካች ሶስት: የምግብ ጥራት
ይህ የምግብ ይዘትንና የአያያዝ ንጽህናን የሚመለከት ሲሆን ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ሞዛምቢክ፣ ቻድ፣ ቶጎ፣ ዛምቢያ፣ ማሊ፣ ናይጄሪያ፣ ባንግላዴሽ፣ ሌሶቶ ከመጨረሻው እስከ አስረኛ ደረጃ ይዘዋል። ኢትዮጵያ በምግብ ጥራት የመጨረሻዋ አገር ናት።
4. አመላካች አራት፡ የሰውነት ውፍረት እና የስኳር በሽታ
ይህ አመላካች ከልክ ያለፈ ውፍረት ዓለም ዓቀፍ የጤና ችግር እየሆነ በመምጣቱ የገባ አመልካች ነው። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥሩ ውጤት ያመጣችሁ በዚህ አመላካች ብቻ ነው። ኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝቧ ቀጫጫ ነው፤ የስኳር በሽታም እንደሌላው አገር የተስፋፋባት አገር አይደለችም።
5. አማካይ ውጤት
የእነዚህ አራት አመላካቾች ድምር ውጤት አጠቃላይ ውጤትን ይሰጣል። በአጠቃላይ ውጤት: ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ አንጎላ፣ ማዳካስካር፣ የመን፣ ቡሩንዲ ናይጄሪያ፣ ሞዛምቢክ፣ ዚምባቡዌ፣ ሴራሊዮን ከመጨረሻ እስከ አስረኛ ወጥተዋል። ኢትዮጵያ ከመጨረሻ ሁለተኛ ነች።
ይህ ምንን ያመለክታል?
ወያኔ ባለፉት አስር ዓመታት በተከታታይ ከ11% በላይ ኢኮኖሚውን አሳድጌዋለሁ ሲለን ነበር። እድገቱ ያተኮረው ገጠር፤ ምንጩም ግብርና ነው ብሎን ነበር። ሐቁ ግን ከላይ የተመለከተው ነው።
እርግጥ ነው የወያኔ ሹማምንት በከተሞች ሕንፃዎችን ይገነባሉ፤ በገጠሮች በመቶዎች ሄክታር የሚለካ ለም መሬት ይዘው ፈጣን ገንዘብ በሚያስገኙ የአበባ፣ የጫትና የቃጫ ምርት ላይ ተሰማርተዋል። ከራሳቸውም አልፈው ሀብታም የውጭ አገራት ሸሪኮቻቸውን በአገራችን ለም መሬት ይበልጥ ያበለፅጓቸዋል። የእነሱ የግላቸው፣ የቤተሰቦቻቸው፣ የዘመዶቻቸው እና የሸሪኮቻቸው ኢኮኖሚ እየተመነደገ መሆኑን እናውቃለን። ይህን በገዛ ዓይኖቻችን የምናየው ሀቅ ነው።
ሆኖም ግን የእነሱ ኢኮኖሚ ማደግ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ አለመሆኑ እናውቃለን። አገራችን ከጓረቤት አገሮች ጋር ስትነፃፀር ወደ ኋላ እየቀረች መሆኑ ያንገበግበናል። በቅርቡ አክስፋም በጥናት ያረጋገጠዉ የኢትዮጵያ ገበሬዎች በየቤታቸው ከወዳጆቻቸው ጋር በምስጢር የሚያወሩትን እውነት ነው።
ከሳምንት በፊት ደግሞ “ኢኮኖሚክ ኢንተለጀንስ ዩኒት” የተሰኘው ታዋቂ የምርምር ተቋም አንድ የጥናት ውጤት ይፋ አድርጎ ነበር። በዚህ የጥናት ውጤት መሠረት በዓለም በከፍተኛ ፍጥነት እያደጉ ያሉ አስር አገሮች በቅደም ተከተል ሞንጎሊያ፣ ሴራሊዮን፣ ቱርክሜንስታን፣ ቡታን፣ ሊቢያ፣ ኢራቅ፣ ላኦስ፣ ቲሞር-ሊስቲ፣ ኤርትራ እና ዛምቢያ ናቸው። በዝርዝሩ ውስጥ ኢትዮጵያ አገራችን የለችበትም።
በዓለም አቀፍ መድረኮችም የወያኔ መረጃዎች ውሸትነት እየተጋለጡ መሆናቸው በጎ ምልክት ነው። የሚያሳዝነው ግን ይህንን ሀቅ የሚያዉቁ ምዕራባዉያን ለጋሽ አገሮች አሁንም ወያኔን እየረዱና እየደገፉ ሥቃያችን የሚያራዝሙብን መሆኑ ነው።
ለዚህም ነው ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዘላቂ መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው በአገራችን መሠረዊ የሆነ የአስተዳደር ለውጥ ሲኖር ነው ብሎ የሚያምነው። የወያኔ አገዛዝ በዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እስካልተተካ ድረስ የኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝብ መደህየቱ፤ ጥቂት ሀብታሞች ደግሞ በብዙሀኑ ድህነት መበልፀጋቸው አይቀርም። የወያኔ ውሸቶች ለኢትዮጵያ ድሀ ምግብና መጠለያ አይሆኑለትም። ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም ማምጣት የምንችለው ወያኔን አስወግደን በምትኩ ለሕዝብ ሁለተናዊ እድገት የሚጨነቅ መንግሥት መምረጥ ስንችል ብቻ ነው።
ስለሆነም ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በውሸት እድገት እያደናቆረን፤ በተግባር ግን እያደኸየን ያለውን ዘራፊውን ወያኔን አስወግደን በሕዝብ ነፃ ምርጫ የተመረጠ መንግሥት እንዲኖረን ትግላችን እናጠንክር ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Thursday, January 23, 2014

ሰለ ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ በጥቂቱ …….

ከጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ጋር የቅርብ ትውውቅ እና አባታዊ ወዳጅነት ያላቸው ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም “አገቱኒ” በተሰኘው መጽሐፋቸው ክፉ ቀንን በተመለከተ እልህ እና ስሜታዊነት የተቀላቀለበት አጠር ያለ ትንተና አስፍረዋል፡፡ ከዚህ ፅሁፋቸው አንድ አረፍተ-ነገር መጥቀስ ብችንል “ክፉ ቀን ጥሩ ነው ጀግና ያፈራል” የሚል ጽሁፍ አለበት፡፡ ጭቆና በበረታበት በዚህ በእኛ ጊዜ፣ በዚህ ክፉ ቀን፣ እውነትም አንድ ጀግና ተፈጥራለች፡፡Reeyot-Alemu
ይህ ክፉ ቀን ያፈራት እውነተኛዋ ጀግና ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ነች! ርዕዮት አለሙ በቃልቲ እስር ቤት ሶስት ዓመት ልትደፍን ጥቂት ጊዜያት የቀሯት ሲሆን በዚህም ረጅም የእስር ቆይታዋ በርካታ ፈታኝ ወቅቶችን አሳልፋለች አሁንም እያሳለፈች ትገኛለች፡፡
ያለ ፍትሃዊ ፍርድ ወደ ወህኒ መወርወሯ ሳያንስ በወህኒ ቤት የሚደረግላት አያያዝ እጅግ መድሎ እና መገለል የበዛበት እንዲሁም እንደ አንድ እስረኛ መብቶቿ የማይከበሩበት ሁኔታ ላይ ነው ያለቸው፡፡
ርዕዮት ከሌሎች እስረኞች በተለየ መልኩ ከእናት እና አባቷ ውጭ በማንኛውም የቤተሰብ አባል ሆነ እጮኛዋ እንዲሁም በሌላ ሰው እንዳትጎበኝ ተከልክላለች፡፡ርዕዮት አስጊ ደረጃ ላይ የደረሰ የጡት ላይ ህመም ያለባት ቢሆንም እና ይህንንም በማስመልከት በግሏም ሆነ በቤተሰቦቿ አማካኝነት የህክምና ክትትል እንድታገኝ ለማረሚያ ቤቱ ጥያቄ ብታቀርብም አስፈላጊውን ህክምና እንዳታገኝ ያለህግ አግባብ ተከልክላለች፡፡
ርዕዮት በእስር ቤቱ ለአስተዳደሩ ሰራተኞች ቅርብ በሆኑ እስረኞች ከፍተኛ ዛቻ እና መገለል ይደርስባታል፡፡ በርዕዮት አለሙ ላይ ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው ግን ህገመንግስቱ የሰጣትን የመናገር እና የመጻፍ እንዲሁም ባጠቃላይ ሃሳብን የመግለጽ ነጻነቷን ተጠቅማ ስለእኩልነት፣ ስለፍትህ፣ ስለመልካም አስተዳደር፣ ስለሰብዓዊ መብት እና የመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ በመጻፏ ብቻ ነው፡፡ ሃሳቧን በነጻነት በመግለጿ ምክንያት ርዕዮት አለሙ አሸባሪ ተብላ ተፈርጃለች፡፡
የሰው ልጅ መጎዳት ከምንም በበለጠ የሚያስከፋት ባለ ሩህሩህ ልቧ ይህቺ ወጣት አሸባሪ ተብላ በመጀመሪያ 14 ዓመት ተፈርዶባት የነበረ ሲሆን ምንም እንኳ የሃገሪቱ የፍትህ ስርዓት ነጻነት ጉዳይ አጠያያቂ ላይ የወደቀ መሆኑን ብታውቀውም ይግባኝ በማለት ፍርድቤቱን የሞገተች እና ፍርዱን ወደ አምስት አመት ማስቀነስ የቻለች ናት፡፡ ለርዕዮት አለሙ የአምስት አመት የእስር ፍርድም ፈጽሞ የማይገባ ቢሆንም ይህን ይግባኝ ለሰበር ሰሚ ችሎት አቅርባ ይግባኝ ያለ በቂ ምክንያት ውድቅ ተደርጎባታል፡፡
ርዕዮት አለሙ ያላት ውስጣዊ ጥንካሬ እና ስብዕና እውነተኛ ጀግና መሆኗን ያስመሰክራል፡፡ በቼንጅ መጽሄት እና በአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ በአምደኝነት እንዲሁም በአዲስ ፕሬስ ጋዜጣ በዋና አዘጋጅነት የጋዜጠኝነት ስራ ስትሰራ የቆየች ሲሆን እስከታሰረችበት ጊዜ ድረስ ደግሞ በፍትህ ጋዜጣ ቋሚ አምደኛ ሆና በርካታ ጽሁፎችን ጽፋለች፡፡
በተጨማሪም በ96.1 ኤፍ ኤም ራዲዮ ላይ ከጓደኛ ሽለሲ ጋር በመሆን በሀገሪቷ የትያትርና ስነጥበብ እድገት እና ተግዳሮቶች ዙርያ ሳምንታዊ ፕሮግራም ታዘጋጅ ነበር፡፡
ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ሁለገብ ጸሃፊ ስትሆን ከኪነጥበብ ጉዳዮች ጀምሮ ፓለቲካዊ ነክ ጉዳዮች ላይ መልካም አስተዳደርን በተመለከተ፣ ስለእኩልነት፣ ስለ ፍትህ፣ ስለ ዴሞክራሲ እና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮችም ዙሪያ በርካታ ጽሁፍ አቅርባለች፡፡ ርዕዮት ጽሁፎቿ ቅንነት የሚታይባቸው ሲሆን ለእውነት፣ ለሰው ልጅ እኩልነት፣ እንዲሁም ለሃገር አንድነት ያላትን ብርቱ አቋም በጽሁፏ ታንጸባርቃለች፡፡
የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ስራዎች በአጠቃላይ ተሰብስበው የኢህአዴግ ቀይ እስክርቢቶ በሚል እርዕስ በመጽሐፍ መልክ የታተሙ ሲሆን በህብረተሰቡ ዘንድ በስፋት እየተነበበ ይገኛል፡፡ ርዕዮት ከጋዜጠኝነት ስራዋ በተጨማሪ ትጉህ መምህር ስትሆን በተማሪዎቿም ሆነ በስራ ባልደረቦቿ ዘንድ የተከበረች ባለሙያ ነች፡፡ከስራዋ ጎን ለጎን ትምህርቷን በመቀጠል ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በአንድ ጊዜ ሁለት ዲግሪ በውጭ ቋንቋዎች እና በትያትር ሰነጥበብ ትምህት ተመረቃለች፡፡
ለወትሮው ዘወትር ጥር 13 ቀን በወዳጅ ዘመዶቿ ተከባ ልደቷን በደመቀ ሁኔታ ታከብር የነበረችው ርዕዮት አለሙ ያለፉት ሁለት አመታት ልደቷ የተከበረው በቃልቲ እስር ቤት ደጃፍ ነው፡፡ ቤተሰቦቿ፣ የሙያ አጋሮቿ እና ጓደኞቿ በተገኙበት ባለፉት ሁለት ዓመታት በቃልቲ እስር ቤት ደጃፍ ልደቷ ሲከበር ርዕዮት አለሙ ምንም የመከፋትም ሆነ የሃዝን ምልክት ሳይሆን የታየበት እንዲያውም ከሌላው ጊዜ በበለጠ ደስተኛ እና ፍልቅልቅ ሆና ነው ያከበረቸው፡፡ የአሁኑ የርዕዮት አለሙ ልደት በቃልቲ እስር ቤት ደጃፍ ብቻ ሳይሆን የሚከበረው በተለያዩ ቦታዎች እና ሃገሮች የጋዜጠኞች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በተሰባሰቡበት በክብር እና በደመቀ ሁኔታ ነው፡፡
የርዕዮት አለሙን የልደት በዓል በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለማክበር ቀደም ብለው በተለያዩ ማህበራዊ ድረ-ገጾች እና ሌሎች ዌብ ሳይቶች እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን ለዚህም በመላው አለም የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያዊያን፣ የኢትዮጵያ ወዳጆች እና የጋዜጠኞች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች አወንታዊ ምላሻቸውን እና ድጋፋቸውን ሰጥተዋል፡፡ለርዕዮት አለሙ ልደቷ በመላው አለም ዙሪያ መከበሩ የሚገባት እንጅ የሚያንሳት አይደለም፡፡
ስለ ሰብዓዊ መብት፣ ስለ እኩልነት፣ ስለመልካም አስተዳደር እና ስለ ፍትህ በመጻፏ እና መንግስትን አጥብቃ በመሞገቷ ያለ ሰሟ ስም ተሰጥቷት አሸባሪ ተብላ ያለ አግባብ ፍርድ አምስት አመት ተፈርዶባት በቃልቲ እስር ቤት መስዕዋትነት እየከፈለች ትገኛለች እና! ምንም እንኳ በእስር ላይ የምትገኝ ቢሆንም እና አሁን ያለችበት ሁኔታ አስከፊ የሚባል ደረጃ ላይ የደረሰ ቢሆንም ለርዮት አለሙ የልደት ቀኗ ነው እና እንኳን አደረሰሽ ለማለት እንወዳለን፡፡

The professional hyenas and the Ethiopian Jungle economy: what is all the fuss about?

የአይጥ  ምስክር  ድንቢጥ?
by Teshome Debalke
Ever since the ruling Regime of Ethiopia came to power it has been confusing the hell-out the world what policy it follows.  It combined the left and the right and Western and Eastern with touch of Ethnic Federalism and Mafioso type jungle economy and managed to stay alive robing the nation blind.  In a matter of a decade, the ragtag guerilla group known as Tigray People Liberation Front (TPLF) ruling Ethiopia admittedly controlled the mainstay of the economy and bragging double digit growth on the way to offshore banks.Ever since the ruling Regime of Ethiopia came to power it has been confusing the hell-out the world what policy it follows.
Don’t get me wrong, any economy will grow when you pump billions of dollars of public money, foreign aid and loan, remittance, and investment. The question is by how much, for whose benefit and expense? That is where the professional hyenas come-in to put their skills at work to legitimize the jungle economy and TPLF’s robbery. Unfortunately, they only appear on ‘don’t ask don’t tell’ Medias controlled by the regime or operated by the professional hyenas themselves.
More fascinating is the duplicity of the professional hyenas in-and-around the Regime double-talking to cover-up the racketeering TPLF is running. For sure, it doesn’t require much knowledge to figure out the jungle economy from real one.  But yet, the modern-day hyenas kept putting out falsehood to tell the world it is the best thing since the slice of bread.
Now, stupidity has no virtue and criminality has no honor, then, why is it the professional hyenas insulting the people of Ethiopia?
There are two possibilities ‘professionals’ in general put their repetition online to vow the jungle economy and TPLF’s robbery is legitimate.  They either have self-interest on the outcome on the expenses of the people or they are ‘functionally illiterate’ to understand how an economy works.
The fact the ruling party is ransacking the public resource to itself and cronies at will is enough to prove the economy is jungle economy–nothing more than a pawn shop owned and operated by TPLF.  But yet, the professional hyenas conspire to claim there is a functioning government posed as Federal, Revolutionary Democracy or Developmental Democracy… that is managing a ‘growing and transforming’ economy in their cut-and-paste exercise of the make-believe world they created to cover up a racketeering ring.
To add to the insult, they mask the fact public institutions are full of mindless cadres– rubberstamping the regime’s misinformation and order while private and civic institutions are taken hostage by TPLF’s hit men posed as government officials, security personnel, investors …
For instance, the institutions of higher education are filled with incompetent cadres masquerading as professors, lecturers and researchers– recycling the regime data and generating falsified papers to validate the regimes cooked numbers. Instead of nurturing and cultivating the mind of the youth to produce problem solvers and entrepreneurs Higher Education Institutions turned into recruitment centers for ethnic cadres and Diploma factory to dispense fake credential to justify filling public institutions with idiotic cadres. Indecently, the top dogs of the regime are all over the cyberspace to acquire credential online as quickly they can print them to join the jungle economy…
Likewise, the institutions of Media that are entrusted to inform and protect the publicinterest fallen on the hand TPLF cadres–parroting the regime’s propaganda to legitimize the jungle economy…to feed the population falsehood, unverifiable blather and diversion.
Pick one or another Media out of the pack you will find professional hyenas pushing baseless propaganda–sugarcoated the jungle economy to entice the gullible to dole in more money while diverting the public attention from the regime’s corruption and atrocities.
Take Addis Fortune , the most quoted business weekly on the international media as an example. The fact it calls itself ‘the largest English weekly in Ethiopia’ circulating few thousands papers in a nation of 90 million not only says it isn’t a Media as it claims but it is in the business of insulting the public’s intelligence. In reality, it’s only job description is to legitimize TPLF led EPDRF government’s jungle economy for theforeign community and the Diaspora–recycling propaganda from the source.
How a legitimate business Media could ignores TPLF’s unprecedented corruption and extortion of the public and private sector and claim it is the largest English Business Weekly? It speaks volumes how far the professional hyenas are willing to be accessories to the crimes of the regime against the people of Ethiopia.
Institution of commerce and trade are also taken hostage by professional hyenas of the regime– forced to swear the propaganda as kosher.   Take for instance Addis Ababa Chamber of Commerce or Ethiopian Chamber of Commerce.  Not a word of TPLF led regime’s crime against the private sector or its racketeering business ever mentioned by both the Chambers that supposedly protect the integrity of the market and the interest of their members from the policy of the ‘regime’ that run the largest business cartel in the nation.
It is abundantly clear by now the economic, as well as the social and political crises of Ethiopia began and will end when the professional hyenas that validate the jungle economy, the jungle justice, the jungle politics … ‘Face the Nation’ and pay for their conspiracy to commit crimes. As the accessories of the biggest heist in the history of the nation they surly are counting their days waiting to face real justice. Unfortunately, they still are roaming the street and appearing on Media talking absolute rubbish.
Donor Group and International Development Agencies weren’t spared from the professional hyenas’ diversion. Closer examination reviles the professional hyenas are well situated in key positions to distract the international community from finding out the reality.
For instant The UK Department for International Development Press Release titled –‘Ethiopia: Economic Development – The Good News From Ethiopia, and What Might Make It Even Better’ sums up the narrative the crime of the regime presented as a good news, thanks to the extraordinary effort of the professional hyenas.
To make matter worst, the British government agency doesn’t even acknowledge the presence of unprecedented crime of corruption of the ruling party. Nor the Agency cared less when UK laws on corruption are violated while it is funding and praising the regime that runs shadow private corporations within its jurisdiction. And yet, the same Agency expects ‘committed, credible and capable’ government and ‘policymaking that is driven by evidence’ from the ruling regime of Ethiopia. It must be either complete insanity of the century or designed to legitimize a lawless regime acceptable for Ethiopians.
Where in the real world a Mafia regime soaked in corruption-running racketeering expected to deliver policy that is driven by evidence is the million dollar question the professional hyenas and their partners in crime must answer sooner or later.
Look my people call it anything you wish and for whatever reasons but, the Ethiopian Ruling Regime is noting that resemble a government, not even by African standard. Therefore, the hype about Revolutionary Democracy, Developmental State, and Growth and Transformation Plan or Millennium Grand Project are all to cover up racketeering rings that are robbing the nation never seen in the modern history of Africa.
Unfortunately, speaking the truth can get me charged as terrorist in the jungle justice, convicted in the kangaroo court and crucified by the propaganda machines while the professional hyenas manufacture the evidence. Regardless, my job is to collect the evidence to expose them until we meet in the real court of justice in the free and democratic Ethiopia.
When all the crimes aren’t sufficient burden on the people of Ethiopia ‘independent professionals’- scholars, researchers, journalists, educators… that supposedly stand guard in the public interest failed to confront their counterpart head-on. Instead, they either are silent chitchatting behind close doors or generating water-down research, reports, articles, news… on issues that doesn’t address the fundamental problem of tyranny.
Take for instance the recently published essay titled ‘From Economic Dependency and Stagnation to Democratic Development StateEssays on the Socio-political and Economic Perspectives of Ethiopia’’ authored by Desta, Asayehgn, Ph.D.

From the outset, I didn’t read the whole essay thus, I can’t comment on the content or the methodology. Nor I know the author’s background and what he contributed to the knowledge base in ‘sustainable economic development’ to earn him the ‘distinguished Professor of sustainable economic development’ in the Dominican University of California.
But, the loaded title misleads and tells the story of our contemporary professionals in general—measuring performance starting from the wrong premises and in the wrongcontext — skipping the fundamentals of governance and institutional transparency.
The title of the essay entails, Ethiopia is graduating ‘from economic dependency and stagnation’ into some kind of ‘Democratic Developmental State’. Thus, the question is, can the process of measuring development under a regime that is running parallel state and corrupt business cartel as it is evident in Ethiopia acceptable and valid?  A simple inquiry of the ruling regime’s business holdings would disqualify the regime as a government running State to reject entertaining to measure a transition to ‘Democratic Development State’ but more like a Mafia Development State’
Therefore, given the reality on the ground, the appropriate title for an essay that attempt to measures transition of the Ethiopian political economy should read‘From Command economy of stagnation and dependency to Mafia Developmental StateEssays on the reality and the hype of transition to Democratic Development State on the Socio-political and Economy of Ethiopia’
Such title would explore and expose the true nature of the new breed of the Mafia regime that took the worst of the command economy and the free economy posing as Revolutionary Democracy or Democratic Development State — promising trickledown benefits for the rest to sustain its rule and robbery.
Again, since I didn’t read or intend to read the entire essay I will leave examining the content and the methodology better equipped ‘professionals’. But, the general fear or capitulation of our contemporary professional elites failing to grab the ‘bull on its horn’ left the people of Ethiopia for ruthless and corrupt regimes playing cat-and-mouse.
Often well intention professionals dive into the hype and create more confusion knowingly or unknowingly legitimize racketeering as acceptable form of governance to base their study. Unfortunately, the world is plenty of such studies that start without addressing the lack of institutional transparency rendering the findings useless in the real problem solving.
The conventional meaning of ‘developmental state’ says
‘Developmental state, or hard state, is a term used by international political economy scholars to refer to the phenomenon of state-led macroeconomic planning in East Asia in the late twentieth century. In this model of capitalism (sometimes referred to as state development capitalism), the state has more independent, or autonomous, political power, as well as more control over the economy. A developmental state is characterized by having strong state intervention, as well as extensive regulation and planning.’
It simply means measurable and verifiable actions a ‘States’ would take to achieve thedesire goals to jumpstart an economy.  What it doesn’t say is a state within a state where the ruling party run both as well as racketeering business–channeling resources to it businesses to dominate the economy as it is the case in Ethiopia.
Here is where professional hyenas are attempting to pass the jungle economy where the ruling party corrupt cartel running amok as acceptable way of governance while independent professionals  going along with the hype–afraid of confronting it head-on.
No one knows how the hyenas came up with the idea that a ruling party can run a government, private businesses and non-governmental organizations and control the public resources to dispense it at will can be called Democratic Development State is beyond me.
It reminds me of what is referred as ‘voodoo economics’ (a negative term that is used to describe any prescribed economic action where the predicted future outcome is not directly traceable to that action).  In Ethiopian case, Developmental State resemble more like voodoo economics of feeding TPLF’s cartels and expecting trickle down economic benefits for the rest.
It also reminds me of Professor Gorge Ayittey, the distinguished Professor of Economics at American University and the Director of Free African Foundation, and critic of African intellectuals. He refers them as ‘intellectual prostitutes’ for those covering up for African dictators and ‘functionally illiterate intellectuals’ for those failing to come up with the solution for African problems. As harsh as it sounds, the problems and the solutions of Africa in general remain on the hands of the intellectuals.
The cow and sausage story of a frustrated father that felt he wasted his money sending his son to America to study sums up the narrative of ‘functionally illiterate intellectuals’.  Upon completion of his studies the son returned home with advance degree.  Unable to find a job that meets his qualification from American University for extended period he continued blaming his country’s backwardness to provide him a job that meets his expectation. Every day, around the dining table, he tells his family the technological advancement of America verses his country. One day he told a story he observed where ‘a cow goes at one end of the factory and turn in to sausage at the other end’. The father, listening in frustration another of his story responded  with  his own dilemma of putting sausage on one end of the factory and getting a cow on the other—referring to his ‘functionally illiterate’ son.
For the most part, it appears our contemporary professionals fall between ’intellectual prostitutes’ or ‘functionally illiterate intellectuals’.  On one side there are those putting their profession out for the highest bidder all together as the professional hyenas do. On the other are those afraid to exercise their profession and others that feel the people and the country that educate them owe them as many independent professional do-leaving the people of Ethiopia for the hyenas of tyranny. They are increasingly becoming nauseous society as well as an obstacle for freedom and democracy.
Because of the silent majority intellectuals (the no-see-and-hear evil group) the people of Ethiopia are paying dearly.  The tragedy is those that sold their profession and dignity for highest bidder seems to have an open season on the people of Ethiopia without contest. Where is the justice in that?
Good examples of professional hyenas are those that appear on regime controlled Media to promote the jungle economy as real and the empty growth and transformation hype and Woyane’s highway robbery as acceptable.  They come as journalist, researcher, consultant, businessperson, investors or expert of one thing or another.
Likewise, good examples of ‘functionally illiterate’ professionals are those that couldn’t have principled stand on the public interest to go after the professional hyenas thus tyranny.
In all honesty, I am an admirer the professional hyenas’ dedication for distraction and corruption. The fact they are willing to be accessory to the heinous crimes of the ruling regime says a lot about their dedication for distraction and corruption many lack for good causes.   I don’t believe money alone is enough incentive for such level of dedication for distraction.  Whatever motivates them to bleed their people and country; we could all learn dedication from them to bring about freedom and democracy to our people.
In any self-respecting government, professional hyenas would be stripped of their credential for breach of professional ethics, charge for perjury and conspiracy to commit fraud… as accessories for crime of corruption… to end up losing their job or and going to jail in disgrace.  But, in the lawless nation of Ethiopia they are praised as heroes of Revolutionary Democracy and appear on public events and on the Media as experts, investors, consultant, and businesspersons.
What Ethiopians can do to bring about the people’s government?
Often Ethiopians see the struggle to rid of tyranny rest with the political leaders of the regime.  Quite to the contrary, there must be an all-out war on the professional hyenas in-and-around the regime.  For example, following the professional hyenas–sniffing around to strangle the means-and-ways of the economy to legitimize the jungle economy leads to the most elaborate network of professional hyenas’ syndicates around the world.
Therefore, like any self-respecting people do, confronting the professional hyenas network behind the regime that legitimize the jungle economy in a cover of jungle justice, jungle politics… to ‘Face the Nation’ is the most important and the shortest known method to end the racketeering ring that finance and sustain tyranny. But, the job requires independent professionals to step out of their hiding and help coordinate the struggle in their own profession– Medias, education, health, law, economy etc.  The silence and timidity not showing as much dedication for a good cause as professional hyenas do for distraction remained the obstacle to end tyranny sooner and must be challenged.
Most importantly, Ethiopians in general and the young in particularly must reject anything tyranny and, collectively call on the silent professionals to step out of their hiding. If knocking doors is required it must be done. Demand transparency from one-and-all–starting from the professional hyenas in-and-around the regime that carries tyranny on their shoulders must be confronted.
Democracy and the rule of law is about accountability, there is no way around it. We know Woyane tyranny and its professional hyenas are accountable for no one but their pocket book. What we want to know is, are all others accountable to the people of Ethiopia or someone else?
When Ethiopians break the silence to demand accountability from one-and-all Woyane tyranny will end in a matter of days and the hyenas behind it will disappear in the darkness; unfortunately with our money.
That is preciously why accountable and transparent Medias and advocacy groups are needed now than ever to go after the professional hyenas of Woyane and everybody else. Those that retreat to ‘Face the Nation’ are no good for our people.  As they say, that is the honest truth you can take to the bank.
AgainEthiopian Satellite Television/Radio is the best thing that happened to Ethiopians. Anyone that tells you otherwise is hiding something not ‘Face the Nation’. I highly recommend a program called “Face the Nation” to start soon to knock on the doors of the hyenas and the rest.
In conclusion, as professional hyenas scramble to save the regime goes on, a short note of warning for all involved in sustaining a dying regime for momentary $$ and self -interest reasons is order.  I suggest looking at the realities around you to find your way out as your masters in TPLF are looking for fall guys as they are shifting money, family members and more to leave you behind for the Day-of-Reckoning coming soon.  Time is running out for the regime and your likes, you might as well make yourselves useful  leaking the information and details that will help speed this collapse and have our motherland Ethiopia have the fresh start her people  yearning for too long.  As the English will say, ‘make your mistakes once or take the money and run’. There is no glory in being accessory for crime against the people.
This article is dedicated to the brave Ethiopian souls languishing in the dungeons of the jungle justice of Woyane. As the hyenas of the regime feast on the blood of the people there is nothing they fear most than the presence of these brave Ethiopians. Make no mistake they are the future leaders of Ethiopia. Woyane stooges will never rest until they surrender for the ideals of these braves Ethiopians.