Monday, March 24, 2014

የሽረ ባጃጆች አድማ መቱ: መንግስትም አገደ

March 24/2014

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

የሽረ እንዳስላሴ ከተማ ባለስልጣናት ከ450-500 የሚሆኑ የባጃጅ ሹፌሮች ሰብስበው ኩንትራት (ኮንትራክት) እየጫናቹ ነው፤ መንግስት የማይፈልገውን አገልግሎት እየሰጣቹ ነው በሚል ሰበብ ማስፈራራታቸው ተከትሎ የባጃጅ ሹፌሮች የስራ ማቆም አድማ በማድረግ ባጃጆቹ ከከተማ ዉጭ በማስቆም ተቃውሞአቸውን እየገለፁ ይገኛሉ። የመንግስት አካላትም አድማው ተከትሎ ባለባጃጆቹ መንግስት ባዘዛቸው መሰረት ለመስራት ፍቃደኛ ካልሆኑ ፍቃድ እንደማይሰጣቸው በመግለፅ እንዳይንቀሳቀሱ አግዷቸዋል። አሁን ባለባጃጆቹ አድማ ላይ ናቸው፤ መንግስትም አግዷቸዋል። በከተማው ምንም የባጃጅ እንቅስቃሴ አይታይም።

ብዙ የከተማው ኗሪዎች ታክሲ አጥተው በመንግስት አካላት ላይ ጫና በመፍጠራቸው ባለስልጣናቱ አምስት ሚኒባሶች ከመነሃርያ የታክሲ አገልግሎት እንዲሰጡ ቢያዙም ህዝቡ በቂ አገልግሎት ማግኘት አልቻለም። ባለ ባጃጆቹ መንግስት መፍትሔ ካልሰጣቸው ሰለማዊ ሰልፍ እንደሚወጡ ለዓረና ፅሕፈትቤት (የሽረ ከተማ ቢሮ) አስታውቀዋል። ከወር በፊት በመቐለ ከተማ ተመሳሳይ ችግር እንደነበር ይታወቃል።
በሌላ ዜና ዓረና ከሀገረሰላም ህዝብ ጋ ተወያየ።
ትናንት እሁድ (መጋቢት 14, 2006 ዓም) ዓረና ፓርቲ በደጉዓ ተምቤን ወረዳ ሀገረሰላም ከተማ ህዝባዊ ስብሰባ አካሂደዋል። ለእሁዱ ስብሰባ ቅዳሜ ቅስቀሳ የተደረገ ሲሆን የሀገረሰላም ህዝብ በጥሩ ሁኔታ ተቀብሎናል።
የህዝቡን ስሜት ያስደነገጣቸው ባለስልጣናት የከተማው ወጣቶች ሰብስበው በስድስት መኪኖች ጭነው ስልጠና አለ፣ ስራ ይሰጣችኋል፣ አበል ይሰጣችኋል ወዘተ በማለት ሕዋነ ወደሚባል ከተማ ሲያጓጉዟቸው አመሹ። ሌሊትም ቁጥራቸው በዉል ያልታወቁ ወጣቶች ሲጓጓዙ አደሩ። ቁጥራቸው ያልታወቀ ወጣቶችም ቅዳሜ ማታ በፖሊሶች እየታደኑ ታስረዋል፤ የዓረና ስብሰባ እስኪጠናንቀቅ ድረስ። ጥረቱ ግልፅ ነበር። ወጣቶቹ በዓረና ስብሰባ እንዳይሳተፉና በአባልነት እንዳይመዘገቡ ለማራቅ ነው፤ ዓረና ከወጣቶች ጋር እንዳይገናኝ ለማድረግ ነው። በብዙ አከባቢዎች በዓረና ስብሰባ የሚሳተፉ ወጣቶች ናቸውና።

ወጣቶቹ ከከተማ በመውጣታቸው ምክንያት የስብሰባው ተሳታፊ ብዙ አልነበረም። ነገር ግን ከብዙ የገጠር ጣብያዎች የተወከሉ አርሶአደሮች፣ መምህራንና የተመሪዎች ተወካዮች ነበሩ። እናም ስብሰባው የተሳካ ነበር ማለት ይቻላል።
አንዳንድ የህወሓት ካድሬዎች (የከተማው የካቢኔ አባላት) በዓረና አባላት ላይ ችግር ለመፍጠር ሞክረው ነበር። አልጋ እንዳንይዝ ባለሆቴሎችን ያስፈራሩ ነበር፣ በአንዳንድ አባሎቻችንም አክታ የመትፋትና የመሳደብ እንዲሁም ለመረበሽ ጥረት ሲያደርጉ ነበር። ግን እነዚህ ተግባራት የፈፀሙ የከተማው የካቢኔ ሐላፊዎች በተናጠል (በግል) የሰሩት እንጂ እንደ የዓዲግራቱ ቀውስ ሆን ተብሎ በፓርቲ ደረጃ የተፈፀመ አልነበረም። ምክንያቱም በሀገረሰላም ካድሬዎች ችግር ሲፈጥሩ ፖሊስ ያስቁመው ነበር። በዓዲግራት ግን ፖሊስ የችግሩ ተሳታፊ ነበረ።
እሁድ ጧት ስብሰባ የጠራንበት የከተማው ማዘጋጃቤት በፖሊሶችና ካድሬዎች ተከቦ ለስብሰባ የመጣ ህዝብ ለማስፈራራት ጥረት ተደርጓል። ብዙዎች እንዲመለሱ ተደርጓል። ባጠቃላይ የህወሓት ባለስልጣናት በዓረና አባላት ላይ ይፈፅሙት የነበረ ግፍ ወደ ተሰብሳቢው ህዝብ አሸጋግረውታል።

አሁን ጥቃት የሚፈፀመው በዓረናዎች ሳይሆን ጥያቄ በሚያነሳና በዓረና ስብሰባ ለመሳተፍ ፍላጎት ባለው ሰለማዊ ህዝብ ላይ ነው። የህዝብ የመሰብሰብ መብት እየጣሱ ነው ማለት ነው። የደጉዓ ተምቤን ህዝብ ለውጥ እንደሚፈልግ አረጋግጦልናል።

Ethiopian Regime Detained Opposition Party Leader, Terrorized Semayawi Party Members

March 24, 2014
Mr. Yilkal Getnet, chairperson of the rising Ethiopian opposition Semayawi Party
Mr. Yilkal Getnet
Ethiopian American Council (EAC)
Silver Spring, Maryland, March 23 – Just before boarding time last Friday night, airport personnel told Mr. Yilkal Getnet that he was to report to a Tigrayan Peoples Liberation Front (TPLF) officer at Bole Airport, Addis Ababa, Ethiopia. Mr. Getnet, chairperson of the rising Ethiopian opposition Semayawi Party, was leaving Ethiopia to attend a Young African Leaders Initiative (YALI) fellowship program in the United States.
Mr. Getnet’s luggage was removed from the plane and he had to endure three hours of intense questioning by some TPLF so-called “security agents” which caused him to miss his flight. Mr. Getnet, educated as a civil engineer, returned to his home around 2 a.m. Saturday morning.
The TPLF government insists that it is a democratic nation concerned with only the best interests of the Ethiopian people. Yet the current regime has no qualms about denying a basic human right – the liberty for a citizen to freely move about and travel to any country he or she desires. Perhaps America is secretly forbidden to young Ethiopian leaders by the ruling government, fearful that these young people may learn too much about democracy and a free citizenry.
YALI was initiated by American President Barack Obama in 2010. He wanted a program, set up through the U.S. State Department, to strengthen young African leaders as they “spur growth and prosperity, strengthen democratic governance, and enhance peace and security across Africa.” Because of the TPLF actions that stopped Mr. Getnet’s travel, these high goals must be troublesome to the corrupt ruling regime.
The ruling powers in Ethiopia can still claim the U.S. as an ally. But, the present regime should be wary about preventing a young Ethiopian from visiting American shores to learn about economic growth, commercial prosperity, and human rights. President Obama set up this program himself. Surely he and his state department, along with American citizens in general, will finally see the farce in this alliance with a dictatorial regime that tramples the rights of its citizens. As of yet, no comment has come from either President Obama or the U.S. State Department regarding Mr. Getnet’s detention.
This is not the first incident in 2014 that marks the repression and terror the current regime has visited on Semayawi Party members and their supporters. In early February, 14 were arrested in the city of  Gondar as they planned a peaceful demonstration to take place in the city’s Mesqel Square. Four executive leaders were among them: Getaneh Balcha (Organization Affairs), Yidenkachew Kebede (Legal Affairs), Berhanu Tekeleyared (Public Relations), Yonatan Tesefaye (Youth Affairs). Two drivers and a camera man were also arrested. Cameras and laptop computers were confiscated.
More recently, Semayawi Party members were arrested and some badly beaten during a protest at a 5k Women’s Great Run event. The women runners used the event to protest the strangle-hold the ruling regime has on the liberties of the Ethiopian people. As is standard with terrorist organizations, the regime’s goons took the women away in the night for interrogation and threatened them with guns held to their heads.
Other parties in opposition to the current regime’s tyranny exist, such as the Andinet and the All Ethiopian Unity Party (AEUP). The Semayawi Party is distinguished by its youthfulness. Most members are under the age of 35 and seem somewhat fearless in the face of state police brutality and the regime’s terrorizing of its own citizens.
The Semayawi Party, also known as the Blue Party, became part of the opposition front during June of last year when a huge rally formed in Addis Ababa. Demonstrators were protesting the unlawful jailing of journalists, and religious and political leaders..
When a regime bans or restricts social media and confiscated cell phones, that is evidence that the regime is restricting or banning the rights of its populace to free speech and other civil expression.
Among other crimes, the current regime is evicting people from their heritage lands and leasing thousands of acres to foreign  corporations – regime cronies pocket the monetary reward. Corruption and poverty presently are endemic in this ancient land and the populace at large deeply resents the ruling regime. The Semayawi Party hopes to forge a unity with other opposition parties, and the Ethiopian populace, to bring about the necessary political change that will allow a truly democratic government to prevail and serve the Ethiopian people.
Last summer, Mr. Getnet vowed that if social and economic issues such as unemployment and inflation were not dealt with soon, that his party would organize more protests. “It is the beginning of our struggle,” he said.
Ethiopian Americans Council (EAC)
1659-D West San Carlos st San Jose, Ca 95128 USA
e-mail: EthioAmericans@gmail.com

ኑ! እንዋቀስ፤ ኢህአዴግንም እናፍርሰው! (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)

March 24/2014

(ይህ “ኑ! እንዋቀስ” የሚለው ስር ነቀል የለውጥ ጥሪ ቀጥታ የሚያነጣጥረው በኢህአዴግ አባላት ላይ ብቻ ነው፤ አመራሩን በፍፁም አይመለከትም)
ኢህአዴግ ራሱ በይፋ ሲናገር እንደተደመጠው፣ በአሁኑ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር ወደ ሰባት ሚሊዮን ገደማ ደርሷል፡፡ ይህም የአገሪቱ ቁጥር አንድ ግዙፍ የፖለቲካ ፓርቲ ያደርገዋል፡፡ በርግጥ ግዙፍ እንጂ ጠንካራ እንዳላልኩ ልብ ይሏል፡፡ ምክንያቱም ጥንካሬ የሚለካው በአባላት ቁጥር ሳይሆን በድርጅት ፍቅር፣በዓላማ ፅናትና በሚሰጡት ልባዊ አበርክቶ ነው፡፡ እንዲህ ያለ አቋመ-ብርቱነት ደግሞ ድሮ በያ ትውልድ ጊዜ ቀርቷል፡፡ በዘመነ-ኢህአዴግ የተንሰራፋው ጥቅመኝነት (በእነርሱ ቋንቋ ኪራይ ሰብሳቢነት) ብቻ ነው፡፡ ለዚህም በደቡባዊቷ አዋሳ ከተማ ስድስተኛው የድርጅቱ ጉባኤ በተካሄደበት ወቅት፣ አቶ በረከት ስምኦን በብስጭት እየተትከነከነ በደፈናው ለጥቅም ድርጅቱን የተቀላቀሉ አባላት በርካታ መሆናቸውን አምኖ በአደባባይ መናገሩ አስረጂ ሊሆነን ይችላል፡፡ ይህን ንግግሩንም አፍታተን ስናብራራው እንደሚከተለው ሆኖ እናገኘዋለን፡- የግንባሩ አባላት ቁጥር ሰባት ሚሊዮን ገደማ የደረሰው በጥቅም በመደለል፣ በአንድ ለአምስት የጥርነፋ መዋቅር በፍርሃት ተጠፍንጎ በመያዙና በመሳሰሉት ነው (መቼስ አቶ በረከት ከድርጅቱ ጉምቱ መሪዎቹ አንዱ ነውና ዘርዝሮ እንዲያስረዳን
አይጠበቅበትም 


የሆነው ሆኖ አባላቱ እንዲህ የመብዛታቸው ምስጢር የድርጅቱ አምባ-ገነንነት ባህሪይ መገለጫ እንጂ አመላይ አጀንዳ አሊያም
ምትሀታዊ ችሎታ እንዳለው የሚያሳይ አይደለም፡፡ ይህ የትኛውም መሰል ሥርዓት ከተጠናወተው ሁሉንም ከመቆጣጠርና መጠቅለል
(Totalitarianism) አስተሳሰብ የሚሰርፅ ማኪያቬሊያዊ አስተምህሮ ነው፡፡ የሆነው ሆኖ ‹‹አምባገነኖች የአንድ እናት መንትያ ልጆች
ናቸው›› እንዲሉ፤ በ‹‹ቆራጡ መሪ›› ዘመነ-መንግስትም በጊዜው ከነበረው የሀገሪቱ ሕዝብ ቁጥር አኳያ መሳ-ለመሳ ሊባል በሚያስደፍር
ሁኔታ ሳር ቅጠሉ ሁሉ ሰማያዊ ካኪ ለባሽ የኢሠፓ አባል ሆኖ ነበር፡፡ ግና፣ ያ ካኪ ለባሽ ሕዝብ፣ የልቡን በልቡ ይዞ ‹‹ቪቫ መንጌ!›› እያለ
አሳስቆ በስተመጨረሻ ጉድ እንደሰራው ሁሉ፤ ‹‹ይህ የህዝብ ማዕበል…›› ተብሎ በአቶ መለስ ዜናዊ የተሞካሸው የ97ቱ የቅዳሜው መሬት
አንቀጥቅጥ የሰልፍ ትዕይንትም፣ በድጋፍ ሳይሆን በግዳጅ የሰመረ መሆኑን ለማየት፤ አይቶም ለመመስከር ከሃያ አራት ሰአት ጊዜ በላይ
አልወሰደብንም፡፡ እንዴት? ቢሉ በማግስቱ (ሚያዚያ 30) ለተቃውሞ ከወጣው ሕዝብ የቅዳሜዎቹም በብዛት መሳተፋቸውን በራሳቸው
አንደበት ‹‹ትላንት ለቲሸርት፤ ዛሬ ለነፃነት!›› በሚል ሕብረ-ዝማሬ ከአደባባዩም አልፎ ከተማዋን በሚያናውፅ የለውጥ ጩኸት
የመሰከሩበት ‹‹ፖለቲካ›› መቼም ቢሆን አይዘነጋምና፡፡
እንግዲህ ይህ ሁሉ ታሪካዊ ሀቅ የሚገልፅልን አንድ ታላቅ እውነት-በጥቅም እየደለሉ አባልን ማብዛት በክፉ ቀን የማይታደግ መሆኑን ነው፡
፡ ጥቅመኝነት ግፋ ቢል የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ‹‹ፀበል›› ያስጠምቅ፣ ‹ኢህአዴግ ጌታ ነው!›ን ያስፎክር ያሸልል ይሆናል እንጂ
የኢትዮጵያን ትንሳኤ መሻትን አያስቀይርም፡፡ ነብር ዥንጉርጉርነቱን እንደማይለውጠው ሁሉ የኢህአዴግ አባላትም ምንም ቢሆን ምን፣
እንደሌላው ሕዝብ የሀገር አንድነት የሚያሳስባቸው፣ ብሔራዊ ውርደት (ረሀብተኝነት) በቁጭት የሚያንገበግባቸው፣ ከዘውግ ልዩነት
የሕዝብ ለሕዝብ መተማመንና አንድነታዊ ጥንካሬው የሚበልጥባቸው፣ የኃይማኖት ነፃነት የሚያስተቃቅፋቸው… ናቸው ብዬ አምናለሁ፡፡
ምክንያቱም ጥቅመኝነት የእጦትን ክፍተት ለመሙላት ለጊዜው ያሰግዳል እንጂ ክብርንና ማንነትን አስሽጦ በባርነት ቀንበር አያሳድርም-
በተለይም ዥንጉርጉርነቱን ጠንቅቆ ለሚያውቀው ኩሩ-ሀበሻ! 

ደግሞስ ምን ያህሉ አባል ነው፣ የድርጅቱን መታወቂያ በመያዙ ብቻ የረባ ጥቅም ያገኘው? በግላጭ እንደሚታየው በግል ጥቅምም ሆነ በተጭበረበረው የዘውግ ፖለቲካ ሳቢያ ኢህአዴግን የተቀላቀሉ የአብዛኞቹ አባላት የኑሮ ደረጃ ዛሬም እንደ ብዙሃኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ከችግር የመቆራመድ አስከፊ ሕይወት አልተላቀቀም፡፡ ፓርቲውን መታከካቸውም በማይጨበጥና በማይታይ እንቅልፍ የለሽ ሕልም አናውዞ ይበልጥ ደቁሷቸዋል እንጂ በቀን ሶስቴ መመገብ እንኳ አላስቻላቸውም፡፡ ሌላው ቀርቶ የድርጅት አባልነታቸው እንደተርታው ሕዝብ በአድሎአዊ አሰራር መማረርን እንዳላስቀረላቸው በርግጠኝነት መመስከር ይቻላል፡፡
ይህ አይነቱም እርግጠኝነት ነው ‹ኑ! እንወቃቀስ (እንነጋገር)፤ እንተማመንምና ሀገርና ትውልድ እየገደለ ያለውን ፓርቲያችሁን አብረን
ተጋግዘን እናፍርሰው› የሚል የማንቂያ ደውል ላሰማችሁ ገፊ-ምክንያት የሆነኝ፡፡ እናም ድርጅታችሁን ትመረምሩ ዘንድ ወደድኩ፡-
ድርጅታችሁ ሥልጣን ላይ ተፈናጥጦ ባሳለፋቸው ሁለት አስርታት የተጓዘበትን መንገድ በአስተውሎት ብትመረምሩ፤ በእርግጠኝነት እንደ
ግዙፍ ዐለት ካገጠጡ ሀገራዊ ውድመቶች እና ከበባድ ኪሳራዎች ጋር መፋጠጣችሁ አይቀሬ ነው፡፡ ይህም ሆኖ በቅድሚያ በተልካሻ
ፕሮፓጋንዳ ያሰለቸንን የብሔር ጉዳይ (የተወሰኑ ሰዎችን አማልሎ አባል ለማድረግ አስተዋፆ እንዳለው ባይካድም) ወደጎን ብለን፤
የትኛውም ብሔረሰብ ባህላዊ እሴቶቹን ማክበር፣ በአፍ መፍቻ ቋንቋው መጠቀም… የፖለቲካ ፓርቲ በችሮታ የሚሰጠው ሳይሆን፣
የማንም ተፈጥሮአዊ መብት መሆኑን ማስረገጥ አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡ ይህ ማለት ግን የድርጅታችሁ ሀቲት፡- ‹አንዱ በሌላው እድሜውን
ሙሉ ሲጨቆን እንደኖረ፤ ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተለየ እንደሆነ፤ ከብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማችን ይልቅ የክልሉን እንዲያስቀድም
መቀስቀስና መስበክን የብሔር ብሔረሰብ መብትን ማክበር ነው› የሚለውን አምኖ መቀበል አይደለም፡፡ በግልባጩ ስርዓቱ እንዲህ አይነት
ጉዳዮችን ሰማይ ጥግ አጉኖ፣ ሕዝብን ከፋፍሎና በጥርጣሬ (በጎሪጥ) ወደሚተያይበት ጠርዝ ገፍቶ፣ የሥልጣን ዕድሜውን ያራዘመበት
ሁለት አስርታትን ያሳለፈ ስልቱ መሆኑን መረዳት አይሳናችሁም ብዬ አስባለሁ፡፡
ሌላ ሌላውን ትተን እንኳ የኢህአዴግን አመሰራረት ብንመለከት ግንባሩን ከፈጠሩት አራቱ ድርጅቶች መካከል ከሞላ ጎደል ህወሓት እና
ኢህዴን/ብአዴንን እንደ ፖለቲካ ድርጅት መውሰድ ይቻል ይሆናል እንጂ፤ ኦህዴድና ደኢህዴን፣ በህወሓት ‹‹አባ መላ››ዎች እንደ
የፋብሪካ ሳሙና በሚፈለጉበት መጠንና ቅርፅ ተጠፍጥፈው ከተሰሩ በኋላ በኦሮሞና በደቡብ ኢትዮጵያ ተወላጆች ላይ እንደ አለቅት
የተጣበቁ የመሆናቸውን ምስጢር እነርሱም ራሳቸው የሚክዱት አይመስለኝም (ምናልባት በሽግግሩ የመጀመሪያ ዓመት ላይ
እንደአስተዋልነው ከኦህዴድ ይልቅ፣ ኦነግ ኦሮሚኛ ተናጋሪዎችን ወክሎ ቢቀጥል ኖሮ ይህ ጉዳይ በዚህ አውድ ላይነሳ ይችል ነበር፡፡ የሆነው
ግን ተቃራኒው ነው፤ የራሱ የፖለቲካ ቁመናና ራዕይ የነበረው በኃይል ተገፍቶ፤ በምትኩ በሌሎች እስትንፋስ ህልው ሆኖ
‹‹የሚያስተዳድረው››ን ሕዝብና ራሱንም ጭምር ቀን ከሌት ‹‹ከብሔር ጭቆና ነፃ አወጣናችሁ›› ስለሚሉት ሞግዚቶቹ ገድል መተረክን
‹‹ፖለቲከኛነት›› አድርጎ የወሰደው ኦህዴድን ያነገሰ ነውና)
በነገራችን ላይ የፖለቲካ ፓርቲን እንደ ፋብሪካ ምርት ጣጣ-ፈንጣጣው ተጠናቅቆለት ሲያበቃ የመጫኑ አሰራር በሁለቱ ክልሎች ብቻ
ተገድቦ የቀረ አይደለም፤ አጋር ፓርቲዎችንም ይመለከታል፡፡ ከአፋር እስከ ጋምቤላ እና ቤንሻንጉል፤ ከሀረር እስከ ሶማሌ ሲተገበር
በትዝብት የተመለከትነው ጉዳይ ነው፡፡ መቼም ገና ከስር መሰረቱ ‹‹እኛ እናውቅልሀለን!›› በሚሉ ‹‹የፖለቲካ ሞግዚቶች›› የተፈጠረ
ድርጅት በምደባ ቦታውን ያገኙ የአመራር አባላቱን በቅምጥል ኑሮ ከማንፈላሰስ በዘለለ፣ ‹‹እወክለዋለሁ›› ለሚለው ሕብረተሰብ ትርጉም
ያለው ስራ ይሰራል ተብሎ የሚታሰብ አይደለምና ‹በኦሮሚያ ሙስና እንደሰላምታ እጅ መጨባበጥ ተዘውታሪና ተራ ነገር ነው›፣ ‹በአፋር
ባጀት መቀለጃ ሆኗል›፣ ‹በሐረር ቤተሰባዊ ኢምፓየር ተገንብቷል›፣ ‹ቤንሻንጉል በድህነት ማቀቀ›፣ ‹ሶማሌ ክልል የአስተዳዳሪው አብዲ
ርስተ-ጉልት ሆነ› ጂኒ ቁልቋል እያሉ ሮሮዎችን ማሰማት ለውጥ አያመጣም፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ህወሓትን እንደ ‹‹ግል አዳኝ››
በመቀበላቸው ብቻ ‹‹የአስተዳዳሪነት›› ካባ የተደረበላቸው ምስኪን የአመራር አባላት በቀላል ጉዳይ ላይ እንኳ የመወሰን ሥልጣን
የላቸውምና ነው፡፡
ይህ እንግዲህ በቀጥታ ከኢህአዴግ ስነ-ተፈጥሮ ጋር የሚጋመድ ችግር ነው፡፡ ሆኖም የመንግስት ሥልጣን መዘውር ከጨበጠ በኋላ
የጨፈለቃቸውን የዴሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶች ተከትሎ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የደረሱ የአያሌ ሰላማዊ ዜጐች ግድያ፣ እመቃ፣
ከስራና ቤት ንብረት መፈናቀል፣ ስደትን… አንድ በአንድ ጠቅሰን ለማውገዝ ብንሞክር ሰማይ-ብራና፣ ቀይ ባህር-ቀለም ሆነው
ካልተመቻቹልን በቀር የሚደፈር አይመስለኝም፡፡ በርግጥ በኢህአዴግ ውስጥ ታላቅና ታናሽ ንጉሠ-ነገሥት የሆኑት ህወሓትና ብአዴን
ብረት ነክሰው፣ ሳንጃ ወድረው በትጥቅ ትግል ያለፉ ከመሆናቸው አኳያ ለየትኛውም አይነት ቅራኔም ሆነ ልዩነት ከመግደልና መጋደል
ውጪ ያለ ሌላ ሰላማዊ አማራጭ ላይዋጥላቸው እንደሚችል መዘንጋት የለበትም፡፡ ኦነግ ከሽግግር መንግስቱ ከተገፋበት ጊዜ አንስቶ
በኦሮሚያ፣ በአዋሳ፣ በሶማሌ… ግፉአን ያለቁበትን፤ እንዲሁም በድህረ-ምርጫ 97 የታየው የጎዳና ላይ ጭፍጨፋ ይህንኑ ሀቅ ያስረግጣሉ፡፡
ኩነቱም ግንባሩ በመጣበት አይነት የነፍጥ የበላይነት ያለፉት ሶቪየት ህብረት፣ ቻይና፣ ቬትናም፣ ኩባ፣ ኤርትራ ባሉ ሀገራት ከታየው
የሕዝቦች እልቂት፣ የተቀናቃኝ ድምፆች መታፈን፣ የጋዜጠኞች መጨፍለቅ… ጋር ቀጥታ ዝምድና አለው፡፡ እነዚህ ሀገራትንም ሆነ
ኢህአዴግን የተለየ ሃሳብ ለማስተናገድ ትዕግስቱም ፍላጎቱም እንዳይኖራቸው ያደረገው ይህ ከውልደታቸው ጀምሮ ከደም-አጥንታቸው
ጋር የተዋሃደው ተፈጥሮአቸው ይመስለኛል፡፡
በአናቱም ኢህአዴግ ከአባላቱ ይልቅ የአመራሩ ‹‹ፓርቲ›› ብቻ ስለመሆኑ ለመረዳት የውስጥ አሰራሩን መፈትሽ የተሻለ ይሆናል፤
እናንተም በቅርበት እንደምታውቁት በድርጅቱ ያልተፃፈ ሕግ ከላይ ወደታች የሚወርድ መመሪያን ትክክል ሆነም አልሆነ ‹‹ለምን?›› ብሎ
መጠየቅ የሚያስቀስፍ ሀጢያት ነው፡፡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመወያየት መሻት፣ ጥያቄ ማቅረብ፣ ሃሳብን መቃወም፣ ስህተቶችን
ማጋለጥ… አሳድዶ በድንጋይ የሚያስወግር አሊያም ከሀገር ሀገር የሚያሰድድ ታላቅ ጥፋት ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ ይህ ሁናቴም ነው
የአስተዳደር ድክመቶቹንም ሆነ አውዳሚ ጉድለቶቹን በፍጹም ለሕዝብ እንዳይደርሱ ገትሮ መያዝን የማይዘናጋበት ዋነኛ መንግስታዊ ስራ
ያደረገው (የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞችን እና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በውሃ ቀጠነ ወደ እስር ቤት ሲያግዝ መክረሙን ልብ ይሏል)
በጥቅሉ ድርጅቱ ለአመራሮቹ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በተደረገባቸው ዘመናዊ “V8” መኪናዎች እንዲምነሸነሹ እና በቢሊዮን
የሚቆጠር የሀገር ሀብት እንዲዘርፉ የሚያስችል ስልጣን ከማጎናፀፉ ባለፈ፤ እናንተ (ብዙሀኑ አባላት) ያተረፋችሁት ምንድር ነው?
በአነስተኛና ጥቃቅን ከመደራጀት፣ ‹‹ኮብል-ስቶን›› ፈልጦ ከመደርደር የዘለለስ ማን ምን ሊጠቅስ ይችላል? እስቲ! የተራቆተችና በድህነት
ወጀብ የተንገላታች ሀገራችሁን በዓይነ-ልቦናችሁ ለማስተዋል ሞክሩ፡፡ ያን ጊዜም ገና ጀንበር ስታዘቀዝቅ ስጋቸውን ለመቸርቸር ጎዳናዎችን
የሚያጥለቀልቁ እምቦቀቅላ እህቶቻችን፣ ‹‹ማምሻም ዕድሜ ነው›› እንዲሉ የመፅዋች ዓይን እየገረፋቸው በልመና ቁራሽ ሕይወታቸውን
ለማቆየት የሚውተረተሩ አዛውንትና ህፃናት፣ በየጎዳናው በየሰፈሩ ሲንገላወዱ የሚውሉ ስራ-አጥ ወጣቶች፣ በቀን አንዴ ለመመገብ ላይ
ታች የሚማስኑ ለፍቶ አዳሪዎች… ምድሪቷን እንዳጨናነቋት ይገለፅላችኋል፡፡ የዚህ ሁሉ መንስኤም የፈጣሪ ቁጣ ሳይሆን ፅንፈኛው
ድርጅታችሁ በሚከተለው በተግባር ያልተፈተነ (የሀገሪቱን ተጨባጭ እውነት ያላገናዘበ) ርዕዮተ-ዓለም፣ ፖሊሲ፣ አድሎአዊ አሰራር፣
ሙስና እና ለኃላፊነት የማይመጥኑ ‹‹አስፈፃሚዎች›› ችግር ስለመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ጥርጣሬ አይግባችሁ፡፡ እናም ጉዳዩ የሀገር ነውና
በግልፅ እንወቃቀስ (እንነጋገር)፤ ስለምንድነው በአባልነት በምታገለግሉት ኢህአዴግ የሚመራው መንግስት ‹ዛሬም በስኬት ጎዳና
እየጋለብኩኝ ነው› ብሎ እንደ ቁራ እየለፈፈ በተግባር ግን፡- መብራት፣ ውሃ፣ መንገድ፣ ኔት-ወርክ እንደ አደይ አበባ በዓመት አንዴ ብቻ
ብቅ የሚለው? በአገልግሎት ተቋማት መጠቀምስ እንዲህ የአሲምባን ያህል ያራቀው ማን ነው? ፍትሕን የጠሉትን መበቀያ መሳሪያ
አድርገው ያረከሱት እነማን ናቸው? ሰርቶ መብላት የማይጨበጥ ጉም የሆነብንስ በማን የተነሳ ነው? …በርግጥ ይህንን ጥያቄ ለጠቅላይ
ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ብናቀርብለት እንደ መለስ ዜናዊ በተረት መሳለቁ ባይሆንለትም፣ ‹‹ሰለሜ ሰለሜ››ን እየጨፈረ፤
እነ‹‹ሚካኤል ስሁል›› በቀደዱለት ልክ ዳናኪራውን እያስነካው ‹‹ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም!›› ብሎ ከመዘባበት አይመለስም፡፡
መቼስ እንደዚህ ሕዝብ የተናቀ የትም አይገኝም፡፡
ኢህአዴግ መፍረስ ያለበት ለምንድን ነው?
ይህንን አጀንዳ ለማንሳት መግፍኤ የሆነው ከላይ ለማሳያ ያህል የተጠቀሱት ስርዓታዊ ጥፋቶች በግላጭ የመታየታቸው እውነታ ብቻ
አይደለም፤ ይልቁንም ድርጅቱ ከስሁት መንገዱ ለመታረም (ለመታደስ) ፍፁም ዝግ-በር የመሆኑ ጉዳይ ጭምርም ነው፡፡ አዎን፣ እነዚህ
አሁን ሁላችንንም እያማረሩ ያሉ አብዛኞቹ ችግሮች የተከሰቱት አንጋፋው ድርጅታችሁ የ‹‹ኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ
ግንባር›› የሥልጣን መሰረቱን ለማፅናት ይሁነኝ ብሎ ከደፈጠጣቸው መብቶች ጋር ተያይዘው ከመሆናቸው በዘለለ ለኢኮኖሚያዊ
ጥያቄዎች በቂ ምላሽም ሆነ ሁነኛ መፍትሔ የሌለው ፀረ-ሕዝብነቱ የተረጋገጠ፣ ለመታረም ዝግጁ ያልሆነ፣ ተስፋችንን ያሟጠጠ ስርዓት
ስለሆነም ነው፡፡ በ1970ዎቹ መጀመሪያ እነበረከት ስምኦን ልባቸው ከኢህአፓ ለመኮብለሉ አብይ ምክንያት አድርገው ያቀረቡትን ችግር
ታዬ የተባለ ታጋይ ‹‹ሞናሊዛ›› በሚለው ግጥሙ ግሩም አድርጎ ገልጦት እንደነበረ በ1993 ዓ.ም ‹‹ፅናት›› በሚል ርዕስ የተጋድሎ
ታሪካቸውን ባሳተሙበት መጽሐፍ ላይ ተርከውታል፡፡
‹‹አንተ ሌዎናርዶ የሮማ ጅል
የሰራሀትን ልታሻሽል
ልታፈርሳት ልትገነባት
ደግመህ ደጋግመህ ልትሰራት
ሰልሰህ ልትሰራት ስትችል
ጣኦት አደረግካት በሞትህ አጉል አጉል
ለራስህ ፍጡር እግዚኦ ልትል››
ይህ ግጥም በሰፈረበት ገፅ ላይ የተጠቀሰው የግርጌ ማስታወሻ ደግሞ ሊተላለፍ የተፈለገውን መልዕክት እንዲህ በማለት አብራርቶታል፡-
‹‹ታዬ የሚባል የኢህአፓ ታጋይ ‹ራሳችን የፈጠርነውን ድርጅት ማስተካከል አለብን› የሚል እምነት የነበረው ሲሆን፣ ዳ ቪንቺ እራሱ
ለሳላት ሞናሊዛ ፍቅር እንደተማረከ ሁሉ እኛም የፈጠርነውንና የተበላሸውን ድርጅት አመለክነው፤ ማስተካከልም ተሳነን በማለት ፓርቲው
ላይ እምነት ማጣቱን ‹ሞናሊዛ› በሚል ርዕስ በፃፈው ውብ ግጥም ገለፀ፡፡›› (ገፅ 61)
እነሆም አብዮታዊ ግንባሩ፣ ከመስራቾቹ አንዱ የሆነው ኢህዴን/ብአዴን፣ ያን ጊዜ ኢህአፓን መክሰሻ ባደረገበት ‹‹ድርጅታዊ አምልኮ››
ራሱም ተጠልፎ ከወደቀ ዓመታት ነጉደዋል፡፡ ታዬ እንዳለውም መሪዎቹ ኢህአዴግን ናቡከደናፆር አሰርቶት እንደነበረው አይነት እጅግ
ግዙፍ ‹‹አምላክ›› (ጣኦት) አድርገው ሀገርና ሕዝብን እየገበሩለት (እየሰዉለት) ነው፡፡ ርዕዮተ-ዓለምም ሆነ ፖሊሲ (በተለይ መሬትን
በተመለከተ) ‹‹የሚቀየረው በመቃብራችን ላይ ነው›› ሲሉም አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ የትምህርት ፖሊሲውም እንዲህ ትውልድን
እየገደለም እንዲሻሻል ያልተሞከረው በዚሁ እምነታቸው ይመስለኛል፡፡ ይህ ሁኔታም ነው እናንተም የምትስማሙባቸውን ታላላቅ ሀገራዊ
ችግሮችን ለመፍታት ኢህአዴግን ከማፍረስ ውጪ አማራጭ እንዳይኖር ያደረገው፡፡ ከእንግዲህ ወዲያም ከጥፋቱ ታርሞ ለሀገር የሚጠቅም
ዲሞክራሲያዊ የህዝብ ሥርዓት ሊያነበር ይችላል ብሎ ተስፋ ማድረግ ተላላነት ነው፡፡ እንኳን እናንተ ከተማ ላይ የተቀላቀላችሁት አባላት
ቀርቶ፣ ከበርሃ አቅፈው ደግፈው እዚህ ያደረሱት አንጋፋ ታጋዮችና አንዳንድ አመራሮቹም በድርጅቱ ተስፋ ቆርጠው ጥለውት መሄድ
ከጀመሩ ሰንብቷል፡፡ ታጋይ የውብዳር አስፋው ‹‹ፊኒክሷም ሞታ ትነሳለች›› በሚለው መጽሐፏ እውነታውን እንዲህ በማለት ገልፀዋለች፡-
‹‹የድርጅቱ አመራር የወሰዳቸውን የተሳሳቱ እርምጃዎች ቀድሞ ከነበረኝ የድርጅቱ ግንዛቤ ጋር በማጣመር ለዓመታት የታገሉለትንና
የደከሙለትን አባላት በነፃ እንዲንቀሳቀሱ ያላስቻለ ድርጅት፣ ለሕዝብ ነፃነትና ለዲሞክራሲ እታገላለሁ ቢል ከይስሙላ የማያልፍ ከንቱ
መፈክር መሆኑን ደምድሜ፣ ከመጋቢት 5 ቀን 1993 ዓ.ም ጀምሮ ራሴን ከድርጅቱ አገለልኩ፡፡ ይህም በሕይወቴ ጉዞ ዋነኛውና ወሳኝ
እርምጃ ነበር፡፡›› (ገፅ 16)
እንግዲህ ከ1968 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የድርጅት፣ የሴቶች ጉዳይና የመንግስት ሥራዎች ተሰማርታ ልጅነቷን በትግል የጨረሰችው የአቶ
ገብሩ አስራት ባለቤት፣ የውብዳር አስፋው እንዲህ አይነቱን ከባድ ውሳኔ በማሳለፍ ከኢህአዴግ ከተቆራረጠች እነሆ አስራ ሶስት ዓመታት
ነጉደዋል፡፡ በግልባጩ እናንተ ደግሞ እስካሁን ድረስ አንቀላፍታችኋል-ገና አልነቃችሁም፡፡ እናም እውነት እውነት እላችኋለሁ፡- ከዚህ
በላዔ-ሰብ ሥርዓት ለመገላገል የምንችለው፣ ዛሬውኑ ይህንን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ዋነኛና ወሳኝ እርምጃ በቆራጥነት መውሰድ
ስትችሉ ብቻ ነው፡፡ አለበለዚያ…
(የዚህ ጽሑፍ ሃሰበ-መልዕክትን በቅንነት ትቀበሉታላችሁ በሚል መተማመን አፈፃፀሙን፡- በምን አይነት መንገድ ተቀራርበን ልንወያይ እንችላለን? በየትኞቹ ጉዳዮች ላይ መግባባት ይቻላል? ሃሳቡንስ ከግብ ለማድረስ ምን ያህል ጊዜ ይወስዳል? የሚሉትንና መሰል ጥያቄዎችን በሌላ ዕትም ተገናኝተን በስፋት እንመክርባቸዋለን)
አትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊትና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ሰራዊት ወታደራዊ ጥቃት ፈፀሙ።

March 24/2014


የኢትዮጵያን ሕዝብ ከጎጠኛውና ከአሸባሪው የወያኔ አምባገነናዊ ስርዓት ለማላቀቅ የትጥቅ ትግሉን አማራጪ አድርጎ ለሀገርና ለወገኑ መስዋዕትነት ለመክፈል ቆርጦ የተነሳው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር /ኢሕአግ/ ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ከሚታገሉ ድርጅቶች ጋር ውህደት በመፍጠር የፀረ- ወያኔ ትንቅንቁንና ፍልሚያውን አጠናክሮ በመቀጠል በተሰለፈባቸው አውደ-ውጊያዎች በጠላት ላይ ወታደራዊ የበላይነትን በመቀዳጀት የሀገርና የወገን መከታነቱን እያስመሰከረ ይገኛል።

በዚህም መሰረት የጋራ ጠላትን በጋራ ለመደምሰስና የኢትዮጵያን ሕዝብ የመብቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ውህደት በመፍጠር በመጋቢት 12 ቀን 2006 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ጠገዴ ወረዳ ልዩ ስሙ ግጨው በተባለ ቦታ ከወያኔው የሚሊሺያ ታጣቂ ሀይል ጋር ባደረጉት ውጊያ ከፍተኛ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ድል ማስመዝገባቸዉን የድርጅቱ አመራሮች አስታውቀዋል።
በዚህ ውጊያ የሚሊሺያ ሰራዊት አመራር የነበሩት፦


1ኛ. አየልኝ ጫቅሌ 2ኛ. ደጀን ተጫኔ 3ኛ. ተስፉ አያናው የተባሉትን የሚሊሺያ ሰራዊት አመራሮች በመማረክ ስለድርጅቱ አላማና ፕሮግራም በማስተማር ወደ መኖሪያ ቀያቸው እንዲመለሱ ተደርጓል ።


በዚሁ እለትም በተደረገው ውጊያ በቅርቡ የወያኔውን አምባገነን ሥርዓት እድሜ ለማሳጠር ድርጅቶች በአንድነት መስራት አለባቸው በሚል ግንባር የፈጠሩት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ባደረጉት ወታደራዊ የማጥቃት እርምጃ 17 የወያኔ የሚሊሺያ አባላትን ገድለው 14 በማቁሰል እንዲሁም የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ከነመሰል ጥይቶቻቸው ጋር በተጨማሪም 2 ሽጉጦችን በመማረክ በጠላት ላይ ወታደራዊ የበላይነትን በመቀዳጀት አንፀባራቂ ድል ማስመዝገባቸውን የሁለቱ ድርጅቶች አመራሮች አስታውቀዋል።


የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞ ግንባርና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ የፈጠሩት ወታደራዊ ግንባር አብሮ መስዋዕትነት ከመክፈል ባሻገር አምባገነኑን የወያኔ ገዥ ቡድን እድሜ ለማሳጠር ውሕደት ፈጥረው የትግሉን ሂደት ለማፋጠን ከመቸዉም ጊዜ በበለጠ መልኩ ጠንክረው እንደሚሰሩ የድርጅቶቹ አመራሮች ገልፀዋል።

የአንድነት እና መኢአድ ዉህድ ፓርቲ የመድረክ አባል አይሆንም ተባለ

March  24/2014

መኢአድ እና አንድነት መጋቢት 11 ቀን የቅድመ ዉህደት ፊርማ ይፈረማሉ ተብሎ ሲጠበቅ ፣ ከመኢአድ ፕሬዘዳንት አቶ አበባው መሃሪ በተጻፈ ደብዳቤ፣ ላልተወሰነ ጊዜ ፊርማው እንዲዘገይ መደረጉ በስፋት ተዘግቧል። አቶ አበባዉ የቅደመ ዉህደቱን ፊርማ ላለመፈረም ሶስት ያልተፈቱ ነጥቦች የሚሏቸውን ያቀርባሉ። ነጥቦቹም የዉህድ ፓርቲው ስያሜን፣ የመሪዎች መመዘኛን እና አንድነት ከመድረክ ጋር ያለዉን ግንኙነት የሚመለከቱ ናቸው።
አቶ አበባዉ ባቀረቧቸው ነጥቦች ዙሪያ ምላሽ የሰጡት የአንድነት ዋና ጸህፊ አቶ ስዩም መንገሻ ፣ የቀረቡት ነጥቦች ንግግር ተደርጎባቸው ምላሽ የተሰጣቸውና ስምምነት የተደረሰባቸው መሆኑን፣ ወደ 800 ታዳሚዎች በነበሩበት የደብተራዉ ፓላቶክ ክፍል ቀርበው፣ መጋቢት 13 ቀ 2006 ዓ.ም በሰጡት ማብራሪያ አስረድተዋል።
አቶ ስዮም የመድረክና የአንድነት ግንኙነት እንደ ነጥብ መነሳቱ እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። «አንድነት እና መኢአድ ሲዋሃዱ አንድነት እንደ ፓርቲ አይኖርም። ይፈርሳል። ምርጫ ቦርድም ከመድረክ ውስጥ ሆነ፣ እንደ ደርጅት ይሰርዘዋል። ዉህዱ ፓርቲ አዲስ ፓርቲ ነው የሚሆነው። መድረክ ዉስጥ መግባት ካስፈለገም እንደ ገና ሀ ተብሎ ለመድረክ ማመልከቻ ገብቶ፣ ለምርጫ ቦርድ አሳዉቆ ነው የሚሆነው» ሲሉ የአንድነት እና የመኢአድ ዉህድ ፓርቲ የመድረክ አባል እንደማይሆን በግልጽ አስቀምጠዋል። «ይሄንንም የመኢአዱ ሊቀመንበር ጠንቀቀው ያወቁታል» ያሉት አቶ ስዩም በዚህ ረገድ ጥያቄ መነሳቱ ግራ የሚያጋባ እንደሆነ ይናገራሉ።
የዉህዱን ፓርቲ የሚመሩ መሪዎች መመዘኛ ሊኖር እንደሚገባ በአቶ አበባዉ የቀረበውን ነጥብ በተመለከተ አቶ ስዩም አንድነት በዚህ ጉዳይ እንደተስማማ ገልጸዋል። የዉህድ ፓርቲዉን ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመናብርት የሚመርጠዉ ከሁለቱን ድርጅቶች እኩል የተወጣጣ ጠቅላላ ጉባኤ እንደሆነ የገለጹት አቶ ስዩም ፣ «በቅድመ ስምምነት የድርጅቱን መሪዎች አይወሰኑም። የዉህዱን ፓርቲ የሚመሩት ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በጠቅላላ ጉባኤዉ የተመረጡ ናቸው» ሲሉ ስምምነት የተደረስበትን የመሪዎች የመሪዎችን አመራረጥ ሁኔታ አስረድተዋል።
የዉህዱ ፓርቲ ስም ምን ይሁን በሚለው ዙሪያ ስምምነት እንደተደረሰ አቶ ስዩም ይናገራሉ። «እነርሱ መኢአድ/አንድነት የሚል ስም፣ አንዴ ደግሞ የመላዉ ኢትዮጵያ አድነት ፓርቲ (መኢዴፓ) የሚል ስም አቀረቡ። እኛ መኢአድ/አንድነት የሚለው መዋሃዳን አያሳይም በሚል አስልተስማማንም። መኢአፓ የሚለዉን በግማሹ ተቀብለነው «መላው» የሚለው ቃል ወጥቶ «የኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ» ይሁን አልናቸውም» ያሉ አቶ ስዩም በስሙ ዙሪያ የነበረዉን ዉይይት ይዘረዝራሉ። ሲያክሉም «እና ፓርቲ ከሚባል ትግሉ የሕዝብን ጥያቄ ያዘለና ሕዝባዊ በመሆኑ ፓርቲ ከሚለው ቃል ይልቅ ንቅናቄ የሚል እንዲገባበት ፈለግን። በኋላ ግን ሁለተቻንም ሁለት ሁለት ስሞችን እንድናቀርብ፣ አባላትና ደጋፊዎች ደግሞ ስም እንዲያቀርቡ በመጠየቅ፣ የሁለቱ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ በድምጽ ብልጫ ስሙን ይወስን በሚለው ተስማምተን ጨርሰናል» ሲሉ አቶ ስዩም የዉህዱ ፓርቲ ስም ምን ይሁን የሚለዉም ጉዳይ እልባት የተግኘለት እንደሆነ ይናገራሉ።
በአቶ አበባዉ የቀረቡ ሶስቱም ነጥቦች በስፋት ንግግር የተደረገባቸውና እልባት የተገኝላቸው እንደሆነ የገለጹት አቶ ስዮም፣ ሌሎች ንግግር ያልተደረገባቸው፣ ያልተፈቱ ጉዳዮች ካሉ፣ አንድነት ለመነጋገር ምን ጊዜም ዝግጁ እንደሆነ ገልጸዋል። «ከአሁን በኋላ እኛ የምናደርገው ነገር የለም። በአንድ እጅ አይጨበጨብም። እኛ አልተፈቱም የምንላቸው ነጥቦች አሉ ብለን አናስብም። ከነርሱ ጋር ከሁለት አመታት በላይ ነው የተነጋገርነው። አይ ይሄ ችግር አለ የሚሉት ነገር ካለ ያቅርቡና እንነጋገራለን» ሲሉ በአቶ አበባዉ የቀረቡት ሶስት ነጥቦ ምላሽ ያገኙ እንደመሆናቸው፣ ሌሎች በአቶ አበባዉ ደብዳቤ ያልተካተቱ፣ ከዚህ በፊት ስምምነት አልተደረሰባቸው የሚባሉና በአንድነት ዘንድ ያልታወቁ፣ ነጥቦች ከቀረቡ አንድነት ለመወያየት ሁሉጊዜ ዝግጁ እንደሆነ አስረድተዋል። አቶ ስዩም «ኳሷ መኢአድ ሜዳ ላይ ነዉ ያለቸው» ሲሉ አንድነት ከመኢአድ አዎንታዊ ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ የመኢአድን ፋይል ሳጥን ዉስጥ ለጊዜው ከቶ ሌሎች እንቅስቃሴዎች ላይ እንደሚያተኩር አብራርተዋል።
መጋቢት 7 ቀን 2006 ዓ.ም የአንድነት እና የመኢአድ ላእላይ ምክር ቤቶች ዉህደቱ በአንድ ወር ጊዜያት እንዲጠናቀቅ፣ የቅደም ዉህደቱም ስምምነት መጋቢት 11 ቀን እንዲፈረም በሙሉ ድምጽ መወሰናቸው ይታወቃል። አቶ አበባዉ የመኢአድ ላእላይ ምክር ቤት ዉሳኔን ቀልብሰው ፣ በግላቸው ስምምነቱን ላልተወሰን ጊዜ እንዳይፈረም የማድረግ መብት እንደሌላቸው፣ ከመኢአድ አመራር አባላት በኩል የሚነሱ አስተያየቶች እየተሰሙ እንደሆነም ለማረጋገጥ ችለናል። የአዲስ አበባ የመኢአድ ምክር ቤትን ጨምሮ፣ በየክልሉ ያሉ የመኢአድ አስተባባሪዎችና መዋቅሮች ፣ ምክር ቤቱ ወስኖ ስምምነቱ ለምን እንዳልተደረገ እየጠየቁ መሆናቸውንም ለማረጋገጥ ችለናል።
በዚህ ጉዳይ ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ተንታኝ የመኢአድ እና የአንድነት የቅድመ ዉህደት ፊርማ ለጊዜው አለመፈረሙ ጊዜያዊ ስቅታ እንጂ እንደ ትልቅ ችግር የሚታይ እንዳልሆነ ይናገራሉ። «በአንድነት ዘንድ በሩ ክፍት ነው። አቶ አበባዉ ባነሷቸው ነጥቦች ዙሪያ ስምምነት ተደርሷል። የመኢአድ አባላትና ደጋፊዎች ፣ ምክር ቤቱም ዉህደቱን ይፈልጉታል። የዉህደቱ ንግግሩ በችኮላ ወይም ለምርጫ ሲባል የተደረገ ሳይሆን ከሁለት አመታት በላይ የፈጀ ነው። የዉህደቱ እንቅስቃሴ 98% ተጠናቋል» ሲሉ ያስረዱት እኝሁ ተንታኝ የቀረው 2% ፣ አቶ አበባው እንዳይፈርሙ ያደረጋቸው ሌላ ምክንያት ካለ፣ ግልጽ በሆነ መንገድ አቅርበው፣ ውይይት በማድረግ ስምምነቱን ማጠናቀቅ እንደሆነ ይናገራሉ።

Extractive Industries: Transparency Group Rewards Repression


March 20, 2014

Ethiopia Approved for Membership Contrary to Rules

Human Rights Watch
(Oslo) – A prominent international natural resource transparency group has damaged its credibility by approving membership for Ethiopia. On March 19, 2014, the governing board of the Extractive Industries Transparency Initiative (EITI), which promotes openness over oil, gas, and mining revenues, admitted Ethiopia as a candidate country despite harsh government repression that has crushed Ethiopia’s once vibrant independent organizations and its independent media.Ethiopia: Stop Using Anti-Terror Law to Stifle Peaceful Dissent
EITI rules call for candidate countries to make a commitment to meaningful participation of independent groups in public debate on natural resource management. Civil society representatives also sit on a national steering committee for EITI.
“The EITI’s decision to admit Ethiopia without insisting on reforms is an affront to the local activists who’ve been jailed or exiled for calling for a more transparent, accountable government,” said Lisa Misol, senior business and human rights researcher at Human Rights Watch. “With this decision, EITI has thrown its principles to the wind and damaged its reputation as a leading good governance group.”
The decision divided members of the EITI board, which includes representatives of governments, companies, and civil society organizations. It also reversed a 2010 decision by the board to defer membership until a draconian 2009 law, still in effect, that sharply limits the activities of independent groups, “is no longer in place.”
Several exiled Ethiopian and international rights advocates called for conditions to be imposed on Ethiopia’s membership bid, but the board did not reach a consensus on such measures.
Under EITI procedures, Ethiopia has three years to prove compliance with the organization’s standards on revenue transparency and other matters. The board can call for an early review based on poor or deteriorating civil society concerns but has never done so.
“EITI’s leadership had an opportunity to stand up for the core principle that civil society participation is a linchpin of good governance,” Misol said. “Instead, it sacrificed EITI’s credibility by allowing Ethiopia to join the ‘transparency’ club despite intense repression.”

Free Reeyot Alemu, an Ethiopian Prisoner of Conscience



Reeyot Alemu is an Ethiopian school teacher and columnist whose wings have been clipped and her mouth sealed. Reeyot has been in prison, after an unfair trail, for the past 1000 days.
Reeyot, prior to her unjust incarceration, wrote a weekly column for many Amharic-language newspapers. One of the fall-outs of the Arab Spring was that authoritarian governments in the MENA region panicked. As is wont with tyrants, many governments were afraid that the wave of dissent might spread to their country and engulf their regime.
In Ethiopia, Reeyot and four other journalists who were arrested in 2011 and convicted based on a trumped up charge of terrorism. The other journalists are Woubshet Taye, Eskinder Nega, Yusuf Getachew and Solomon Kebede.
On June 21, 2011, Reeyot Alemu was abducted from the high school where she taught English Language. The place of her arrest and the charges for which she was being detained were concealed from her family. According to the Safe World for Women, Reeyot’s dignity was assaulted by Ethiopian authorities for “refusing offers of clemency in exchange for providing information on other journalists, was punished with nearly two weeks in solitary confinement.”
What was Reeyot Alemu’s crime? Safe World for Women explains: “Four days before her arrest, Alemu had written a scathing critique of the ruling political party’s fundraising methods for a national dam project, and had apparently drawn parallels between late Libyan despot Muammar Gaddafi and Ethiopia’s then-Prime Minister, Meles Zenawi.”
Reeyot was held in solitary confinement for three months before her trial, without legal counsel. Her charges were both vague and witnesses sprung from thin air to implicate her. And as though that were not enough, in a pre-mediated media framing, a documentary ran on state television in Ethiopia that painted Reeyot as a terrorist.
Eventually Reeyot was handed a 14 year sentence after a sham trial. In August 2012, the appeal court commuted the 14 years sentence to a five years prison sentence. The court also threw out the terrorism charges against her.
Reeyot Alemu is currently has a tumour in one of her breasts, which is also bleeding. Sadly her condition is without proper medical diagnosis, thus giving great concern about her health conditions. It should be noted that women with malignant breast lumps, in absence of specialized and immediate treatment stand chances of losing a whole breast or even death.
Reeyot deserves to be free; it is not a privilege but a human right. Her dignity has been violated, her voice has been so forcefully silenced and above all her life hangs treacherously on a thin line. Reeyot Alemu, a prisoner of conscience, should be commended not condemned. This woman of valor should be praised not imprisoned. Free Reeyot now before she dies in prison!By Nwachukwu Egbunike