Wednesday, August 27, 2014

ሙስና ለሶስት የሰነጠቃቸው ቡድኖች

ሙስና ለሶስት የሰነጠቃቸው ቡድኖች

August27/2014
ወያኔ ኢህአዴግ በጠመንጃ ኃይል ሥልጣን ላይ ፊጥ ካለ ድፍን 23 ዓመት ቆጠረ፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግ በአንቀልባ አዝሎ ለሥልጣን ያበቃው ዛሬ አምርሮ የሚጠላው ሻዕቢያ ነው፡፡ ወያኔ እና ሻዕቢያ ውሃ በወንፊት እንቅዳ ባሉበት የፍቅር ዘመን እነኢሳያስ አፈወርቂ ኦፊሻል ባልሆነ መንገድ ጥሬ ሥጋ ለመቁረጥ በየሳምንቱ አዲስአበባ ይመላለሱ እንደነበር የቅርብ ሰዎች የሚያስታውሱት ነው፡፡
Muktar-300x142ዛሬስ፤ እነዚህ ሁለት ኃይሎች ለመጠፋፋት የሚፈላለጉ ሆነው ተፋጠዋል፡፡ የሚገርመው ወያኔ፤ የሻዕቢያ ጉዳይ አስፈጻሚ ሆኖ ሀገርን ያህል ነገር ማስገንጠሉን፣ አሰብን አስረክቦ ሀገሪቱን ያለወደብ ማስቀረቱን ጭምር እየረሳ የዛሬ ተቃዋሚዎችን ለምን ከሻዕቢያ ጋር ታያችሁ፣ገንዘብ ተቀበላችሁ እያለ በሀገር ክህደት ጭምር ለመክሰስ ሞራል አግኝቶ ሲወራጭ ማየት ነው፡፡ የትላንቱ የነጻነት ታጋዮች ለሕዝብ ነጻነትና ዴሞክራሲ ታግለናል እያሉ ከ20 ዓመታት ጉዞ በሁዋላ የተትረፈረፈ ነጻነቱን ለራሳቸው ሰጥተው ሌላውን ለመጨፍለቅና ትላንት ባወገዙት የደርግ መንገድ ለመጓዝ አላቅማሙም፡፡
ወደ ሰሞነኛ ጉዳይ እንመለስ ጄኔራል ባጫ ደበሌ አሜሪካን ሀገር ቤት ገዛ የሚል ገራገር ዜና ሰሞኑን በማህበራዊ ድረገጾች ሳነብ አባይን ያላየ ምንጭ ያደንቃል ብዬ በውስጤ አጉተምትሜያለሁ፡፡ የሌባው ቡድን መስረቅን እንደመብት ቆጥሮ በአዲስአበባ ከተማ ቀብረር ያለ ህንጻ በዘመድ አዝማዱ ሰም ሲገነባ ትንሽ እንኳን ሼም እንደሌለው ስትታዘብ ጄኔራሉ በአድራጎቱ አፍሮ ትንሽ ራቅ፣ ደበቅ ለማለት የመፈለጉን ነገር ታመሰግናለህ፡፡ የሌባው ቡድን 5ሺ ብር የማትሞላ ወርሃዊ ደመወዝ ይዞ ልጆቹን በውጪ ሀገር ውድ ት/ቤት ጭምር ሲያስተምር፣ ሚስቱ የሚሊየን ብሮች መኪና ስታሽከረክር፣ ባለቅንጦት ቪላ ገንብቶ ሲንጎማለል ስታይ ጄኔራሉ አንድ ቤት ቢገዛ ታዲያ ምን ይጠበስ ልትል ትችላለህ፡፡ እናም የመከላከያ ወታደሮችን ይጭነቃቸው እንጂ ጄኔራሎቹማ ዛሬ ቢጠሩዋቸው የማይሰሙ ቱጃሮች ሆነዋል፡፡ የሚገርመው ግን እነዚህ ጄኔራሎች ነገ ጥቅማቸውን የሚነካ ነገር ቢመጣ ብረት ላለማንሳታቸው ልማታዊ መንግሥታችንም እንኳን እርግጠኛ መሆን አለመቻሉ ነው፡፡ ኢህአዴግ ነፍሴም «ሙስናን እንዋጋለን» በሚል መፈክር ታጥሮ የሚኖረው ለዚህ ሳይሆን ይቀራልን?!
በአሁን ወቅት ገዥያችን ኢህአዴግ ለሶስት የመሰንጠቅ አዝማማያ እየታየበት ይገኛል፡፡
ቡድን አንድ የደረጀው የሌባ ቡድንን ያቀፈ ነው፡፡ ይህ ቡድን ከፍተኛ መንግሥታዊ ሥልጣኑን የተቆጣጠረ ስለሆነ ጥቅሙን ለማስጠበቅ ማንኛውንም የኃይል እርምጃ የሚወስድ፣ ጥቅሙ ሲነካ ወይንም ይነካል ብሎ ሲሰጋ ሰዎችን የሚያስር፣ የሚያሳድድ የጨካኞች ስብስብ ነው፡፡ እስከታችኛው ድረስ የራሱ መዋቅር የዘረጋና ብዙ ጀሌዎች ያሉት በመሆኑ ተጽእኖው የሰፋ ነው፡፡
ቡድን ሁለት ሟቹ ጠ/ሚኒስትር በአንድ ወቅት እንዳመነው ነገ ይቀናኝ ይሆናል ብሎ የተቀመጠ ተስፈኞች የተሰባሰቡበት ቡድን ነው፡፡ ይህ ቡድን የሌባው ቡድን ስላላስጠጋው አምርሮ እየተቃወመና ብሶቱን እየገለጸ ያለና እንደእስስት ገላውን የሚቀያይር ቡድን ነው፡፡ በተመቸው ጊዜ የሚደግፍ፣ ያልተመቸው ሲመስለው የሚቃወም እበላ ባይ የአደገኛ ሰዎች ስብስብ ነው፡፡ ይህ ቡድን በአመዛኙ በታችኛው እርከን ላይ ተከማችቶ የሚገኝ በመሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በማባባስና በማወሳሰብ ዘወትር ቢወቀስም ምንም ለውጥ ማምጣት ያልቻለ ነው፡፡
ሶስተኛው የኢህአዴግ አባልም ደጋፊም ሆኖ እውነተኛ ዜጋ ሲሆን ሁለቱን ወገኖች የሚጠላ፤ ግን ተጋፍጦ ለመታገል አቅምና ድፍረት ያጣ ነው፡፡
በሒደት አንዱ ነጥሮ መውጣቱ የማይቀር ነው፡፡

( የእኔ የለጣፊው አስተያየት- አጠቃላይ ድርጅቱ የሚጠፋበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም

Disengaging from the False Dilemma of Armed Vs Peaceful Struggle (Professor Mesay Kebede)


Posted by: admin    Tags:      Posted date:  August 26, 2014  |  No comment



Disengaging from the False Dilemma of Armed or Peaceful Struggle
Messay Kebede To Andargachew Tsege
August 26, 2014
The consecutive rise of two dictatorial and sectarian regimes has convinced a great number of Ethiopians that peaceful rather than armed struggle gives the best opportunity for the democratization of Ethiopia. The experience of armed insurgents instituting sectarian and repressive regimes in Ethiopia as well as in other numerous countries, despite their often widely publicized commitment to justice and democracy, has rooted in most Ethiopians the belief that democracy will never prevail so long as armed groups, which by definition are not accountable to the people, become agents of social changes. Instead, what is needed is to organize, educate, and mobilize the people through peaceful struggle and achieve change by their open and direct involvement. In this way, the people retain the control of change and empower political elites that are primarily both accountable to them and representative of diverse interests. Needless to say, proponents of peaceful struggle know too well that the path is bound to be difficult and fraught with appalling pain and sacrifices, obvious as it is that dictatorial regimes will take extreme measures to discourage and defeat such a movement.
G7 Army BBBBBBBLike most people in Ethiopia, I had so far endorsed both the promises of peaceful struggle and its onerous nature without, however, ever condemning or criticizing those who advocate armed struggle. Not only was I convinced that one cannot separate the means from the goal so that only democratic means can lead to democratic results, but also I persuaded myself that the recourse to armed struggle to overthrow the TPLF would be dangerous to the very existence of Ethiopia. Indeed, the ethnic fragmentation of Ethiopia in the hands of the TPLF could only encourage the proliferation of armed groups that would easily take ethnic banners, thereby precipitating the country into a terrible civil war from which it may not emerge as one country.
On the other hand, I was also perfectly aware of the nature of the TPLF. I never shared the illusion that the TPLF will accept the verdict of the ballot-box and step down from power peacefully. That is why I wrote several papers that many commentators and activists either disliked or labeled controversial in which I argued in favor of the establishment of a national government of reconciliation. The proposal was an attempt to lure the leaders of the TPLF into the democratic process by calming their fear of electoral defeat, which would leave them powerless and venerable to a revengeful policy. I found utterly naïve the belief that the TPLF will play the democratic game when it has so much to lose and nothing to gain. Assurance and confidence building through a transitory process in which the TPLF shares power with the opposition appeared to me as the best way to launch the democratization process.
In the face of mounting opposition, the proposal offered an incentive to the TPLF, namely, the opening of the political field in exchange for a guarantee against complete loss and vindictive actions, the result of which would be a win-win situation for all concerned. The TPLF no longer needed to intensify its repressive policy to say in power, which intensification will only lead, sooner or later, to a violent overthrow either by popular uprisings or armed groups. The proposal thus removed the likelihood of a violent overthrow and protected the leaders of the TPLF from political and economic marginalization.
Unfortunately, far from seeking accommodation, all what the TPLF leaders are doing today suggest the recourse to a policy that is set on using all the repressive power of the state to say in power by all means necessary. Recent arbitrary arrests of political leaders and journalists give an unmistakable evidence of the determination to keep power by all means. Add the recent repression to the twenty years of unfruitful peace struggle to have a clear idea of the deadlock of the Ethiopian struggle for change.
In light of this evidence, the question is to know whether peaceful struggle can withstand and eventual defeat a regime that offers nothing but the perpetuation of its absolute power. If one is convinced that the TPLF will never tolerate the rise of a strong democratic opposition, then what is left but the path of a violent overthrow? If the answer is yes––I do not see how a different answer could be possible––what else is endorsed but the inevitability of a violent confrontation whatever form it may take? But then, the inevitability of violence rehabilitates armed struggle, not only as the only recourse but also as the one that offers the possibility of victory. If one is convinced, I repeat, that the TPLF will never give up power peacefully, then one supports the idea that violence is inevitable. Accordingly, it makes no sense to postpone the inevitable confrontation by falsely dissuading oneself that a peaceful victorious outcome is possible for the opposition.
Moreover, while there is no doubt that numerous exceptionally courageous and committed political leaders, journalists, and activists have sacrificed their freedom and life to force the TPLF to be faithful to its own constitution, the downside is that the regime ends up by appearing invincible, thereby discouraging other challengers and plunging Ethiopians in a state of utter resignation and submission for a very long time. There is a limit to what a country can sacrifice without any tangible result.
True, armed struggle is also a very dangerous undertaking, but with the major difference that one is not powerless and can inflict real pain to those who stole others’ freedom. I do not deny that peaceful resistance can prevail over the harshest dictatorial regime given enough time, for no regime is everlasting. Unfortunately, what Ethiopia does not have is precisely time. Ethnic politics is tearing the country apart by undermining, slowly but surely, all the legacies of a common history and shared identity. Whether we like or not, new smaller nations are emerging from the ethnic fragmentation of the country. There is clearly an urgent need to stop the bleeding. What is taking place is as damaging as the direct occupation of the country by a foreign power, which would have naturally given rise to an armed resistance. That the loss of Ethiopia is fomented by treacherous natives should not invite a different reaction.
Above all, it seems to me that the only remedy against the resignation and fatalism that reign in the heart of most Ethiopians is the use of a violent form of struggle. Violence forces us to be free. As Frantz Fanon puts it referring to the colonizer, “the appearance of the settler has meant in the terms of syncretism the death of the aboriginal society, cultural lethargy, and the petrification of individuals. For the native, life can only spring up again out of the rotting corpse of the settler.” What this means is that we need violence, not primarily to overthrow the TPLF, but to be worthy of it, that is, to recover the dignity and anger that make submission unacceptable. To the extent that violence is a provocation of a repressive regime, which naturally reacts by indiscriminate violence, it ends the safety of resignation and fear. It puts everybody in the state of survival by all means and so moves the use of violence from choice to necessity. What Ethiopians need urgently is not so much the recognition as the imposition of freedom by using violence to dissolve the security obtained through submission. Make life dangerous, and you force people to join the fight.
Additionally, those who are hired by the TPLF to terrorize the people and the opposition do so because the absence of armed struggle gives them complete immunity and safety. As soon as they understand that they can become the target of violent reaction, their incentive to kill, torture, and maim diminishes drastically. For them too, the threat of violence has an awakening impact, since they are asked to kill and maim persons who, having ceased to be docile, transform their job into a very risky business. The revelation of their own vulnerability is how they commence to think, thereby recovering what they had exchanged for easy money, to wit, the ability to think critically. They now understand that their job is demanding the sacrifice of their own precious life and that the exchange is utterly unfair.
Last but not least, peaceful struggle has the chance to prevail over the regime if the latter is threatened by violent overthrow. Experience shows that even the fiercest dictatorial regimes suddenly call for dialogue and reconciliation when they feel threatened by armed insurgents. The power of violence makes such regimes suddenly reasonable. What this tells us is that we must drop the either/or reasoning that it is hurting us. By vilifying the recourse to violence, we are doing a big favor to the regime in place. What else could better prolong the life of the regime than the opposition condemning the use of violence? It is my belief that peaceful opposition, which we all want to triumph, cannot do so without the backing of armed insurgency. In other words, we must not see peaceful struggle and armed insurgency as mutually exclusive; instead, we should see them as allies working with different means to achieve the same goal.
This idea of partnership needs to be promoted. All the more so as armed struggle by itself, even if it brandished the goal of democratization, cannot achieve it without the support of an organized people. The irreplaceable role of peaceful struggle is that it organizes and educates the people who are the direct participants. Armed insurgency without an organized people would result in nothing else, despite its generous inspiration, than dictatorial rule. If history teaches us one thing is that democracy cannot be imposed and that those who have tried to do so have become the worst dictators. Democracy works only if the people have the clear sense of being the only source of legitimate political authority and have the means to enforce it, namely, organization and leadership. The triumph of an armed insurgency in a situation where the people show some degree of organization is less frightening and to some extent controllable. Such a people can require that the leaders of the insurgency retain power only under the condition that they win at the ballot box through fair and free elections.
To sum up, the question, armed struggle or peaceful struggle, is a false dilemma. These two forms of struggle are actually complementary. Those who are committed to armed struggle should not denigrate peaceful struggle. On the contrary, they must see it as a necessary component of the democratization goal. Inversely, those who are committed to peaceful struggle must stop demonizing armed insurgency; they should rather view it as a necessary condition for the success of their goal. Instead of either/or, our position must be this and that. Let there be no misunderstanding: what I say does not mean that I am walking away from peaceful struggle. I am firm in my belief that democracy is unachievable without the acquisitions of peaceful struggle. I am simply taking note of the fact that, given the political fragmentation of the country and the nature of the TPLF, peaceful struggle by itself is incapable of bringing the TPLF to the negotiation table. I am also firm in my belief that the only way to institute a genuine democracy in Ethiopia is through the inclusion of the EPRDF in the democratic process, as opposed to its exclusion. I do not see how a commitment to peaceful struggle would exclude the EPRDF without recourse to violent repression. The best outcome for Ethiopia lies in a genuine negotiation between all the concerned forces with the understanding that, given the nature of the TPLF, the use of force conditions the occurrence of said negotiation.

Sunday, August 24, 2014

ሰሞኑን የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ ትኩሳት


IMG_2612ናትናኤል በርሔ ( ኖርዌይ ቲንግቮል)
ለአንድ አገር አስተዳደር መንግስት ለዜጎቹ መሰረታዊ ፍላጎቶች ከሆኑ ነገሮች አንዱ የሆነው ሰው ስራውን ሰርቶ በቂ የላፋቱን ዋጋ ማግኘት መብት ነው በተለይ በአሁኑ ሰዖት መንግስት እከተለዋለሁ ከሚለው መርህ የተገላቢጦሽ እየሆነ ዜጎች በገዛ አገራቸው በተፈጥሮዋዊ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋ የኢኮኖሚ ግሽበት ከድጡ ወደ ማጡ እየተሸጋገሩ ይገኛል።የቀድም ጠቅላይ ሚኒስተር የሽግግር መንግስቱ ሲመሩበት በነበር ጊዜ በዋሽንግተን ዲሲ october 1995 በተጠየቁት ጥያቄ ” የዛሬ 10 ዖመት ወይም 20 ዖመት በሗል ኢትዮጵያ በዚህ ሁኔታ ባየው ደስ ይለኛል ብለው የሚያስቡት” ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ እሳቸው ሲመልሱ የዛሬ 10 ዖመት ይሆናል ብየ ተስፋ የማደርገው እና የምመኘው ሁሉም ኢትዮጵያዊ በቀን 3 ጊዜ ምግብ ያገኛል የሚል ነው።ከዛም ቀጥሎ ምናልባት በጣም የተሳካልን እንደሆን በአመት 2 ቅያሪ ወይም 3 ቅያሪ ልብስ ያገኛል እንዲሁም ከዛ በጣም የተሳካልን እንደሆነ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ህዝብ ግፋ ቢል ከመንገድ 2 ሰዖት ርቀት በላይ ይኖራል።በተጨማሪም የኢትዮጵያ ህዝብ ምግብ አማርጦ ይበላል።ነገር ግን ከ19 ዖመት በፊት የተናገሩት ቃል የተስፋ ቃል ከመሆን ያለፈ እና የዘለል አልሆነም።የኑሮ ውድነቱ ይልቁንስ የታችኛው ክፍል ህብረተሰብ ፈተና ውስጥ እና አደጋ ውስጥ ከቶታል።በተለይ የደመወዝ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ጭማሪው ይመለከተናል የተባለው የመንግስት ሰራተኞች አብዛኞቹ ይጨመርላቸዋል የተባለው ጭማሪ የኑሮውን ሁኔታ ከመቅረፍ ይልቅስ ኑሮው የባሰ የሚያደገረሽ እና ገንዘብ የመግዛት አቅም ያሳጣዋል።መንግስት ከወራት በፊት የደምዝ ጭማሪ አደርጋለሁ በማለቱ ምክንያት በአንዳንድ ምርቱን አምራች ፋብሪካዎች የምርት አቅርቦታቸው ላይ ጭማሪ አሳይተዋል።
በዚህም በተያያዘ ዜጎች፣ገበሬዎች፣ተማሪዎች፣ክሊኒኮች፣ሆስፒታሎች፣ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች የጥራት መጋደል እና በበቂ ሁኔታ ያለመቅረብ ችግሮች ያመጣል።ነጋዴ እና ቸርቻሪ ነን ባዮች ሕዝቡን ጨርቁን አስጥሎ ለመስደድ ቆርጠው የተነሱ ይመስል ከመንግስት ጋር እሽቅድምድም ይዘዋል፡፡ መንግስት ዋጋ ተምንኩ ሲል፣ እነሱ ከላይ ከላይ ዋጋ ይጨምራሉ፡፡ ሸማቹ ግን የእነሱን ጭማሪ ያክል እድገት በየወሩ እንደማያስመዘግብ የታወቀ ነውና ግራ መጋባትን ሲጋፈጥ ይስተዋላል ይህ መተረማመስ ወራትን ተሻግሮ እንደ ከዚህ በፊቱ ድስት ጥዶ የዘይቱን ማለቅ ያየ ሮጥ ብሎ ከሱቅ ማግኘት አልቻለም፡፡ ብዙዎችም ቡና በጨው ሳይወዱ ለመጠጣት ተገደዱ፡፡ ልብሳቸውን በአመድና በእንዶድ ማጠብ እስኪከጅሉ ድረስ የሳሙና ዋጋ የማይቀመስ ሆነ፡፡ አሁን ደግሞ መንግስት የቸርቻሪነትና የአከፋፋይነት መብቱን መንግስት ነክ ለሆኑ ተቋማት አሳልፎ ሰጥቷል፡፡ እውነት ይሄ ግና እስከምን ድረስ ያስኬዳል ?
ለመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ከመደረጉ በፊት ደሞዝ ሲጨምር አብረው ዋጋ የሚጨምሩትን ነጋዴዎች ለመቆጣጠር ተብሎ የዋጋ ተመን መደረጉ በብዙ ሚዲያዎች ተወራ፡ ፡ ደስ ብሎን ሳናበቃ የደሞዝ ጭማሪው ምን ያክል እንደሆነ ሳናውቅ የዋጋ ጭማሪን መንግስት ራሱ አንድ ብሎ ጀመረው፡፡ ማባሪያና ማቆሚያ ያጣው የየወሩ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ያልነካካው ማን አለ?
በመጀመሪያው ወር የትራንስፖርት ወጭው አንድ መቶ ብር የነበረ ግለሰብ፣ በሁለተኛው ወር ወደ አንድ መቶ አስራ አምስት ብር፤ በሶስተኛው ወር ወደ አንድ መቶ ሃያ አምስት ብር፤ በአራተኛው ወር ወደ አንድ መቶ ስልሳ ብር እያደገ ይገኛል፡ ፡ ለመሆኑ የትኛው ኢትዮጵያዊ ሰራተኛ ነው በየወሩ ይህንን ያክል ጭማሪ መሸከም የሚችለው; በደሞዙ ወይም በገቢው ይህን ያክል ጭማሪ መቋቋም የሚያስችል እድገት እያገኘ ያለው የትኛው ሰው ነው? ሁሉም የትራንስፖርት አማራጮች እጅግ እጅግ አስጨናቂ በሆኑበት በዚህ ዘመን በእግር መሄድን ምርጫ ማድረግ የብዙዎች
ግዴታ እየሆነ ነው፡፡
መንግስት ነዳጅ ወር እየጠበቀ የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን ተያይዞታል፡፡ የዚህን ምክንያት በተመለከተ በየጊዜው ምክንያቶች ይደረደራሉ፡፡ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ስለጨመረ የአረብ ሀገራት በአብዮታቸው ምክንያት ያቀርቡት የነበረው የነዳጅ መጠን ስለቀነሰ ወዘተ ይባላል፡፡ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ስለጨመረ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ ቆዳ ከመወጠር ሌላ አማራጭ የለውም ? ለመንግስት ሰዎች ስብሰባ የቅንጦት ውሃና ኩኪስ መግዣ በየጊዜው እንደ ርችት ለሚረጩት የጽህፈት መሳሪያዎች ወይም ለሌላ አልባሌ መዝናኛ የሚወጡ ወጭዎችን ቆጥቦ ነዳጅ ላይ ድጎማ ማደረግ አይቻልም እንዴ ?
የደሞዝ ጭማሪው የተደረገው ለመንግስት ሰራተኞች እንጅ ለሁሉም የሀገሪቱ ሰራተኞች አይደለም፡፡ እንደውም ይህንን ልብ ብለን ከተመለከትነው ከምሬት ብዛት ሊያስቀን የሚደርስ እውነታ እናያለን፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ ተመሳሳይ የትምህርት ደረጃ ኖሯቸው በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ ሁለት መምህራንን ብናነጻጽር፣ ይህንን እውነታ ማየት እንችላለን፡፡ ለነገሩ የግል መስሪያ ቤቶች ጉዳይ አሁንም ስግብግብ ነጋዴዎችን የሚመለከት ቢሆንም፣ ተቀጥረው የሚሰሩት ግን እንደዜጋም፣ እንደነጋዴም፣ እንደሰራተኛም ሊታሰብላቸው ይገባል፡፡
መንግስትም ቢሆን ያደርጋል ተብሎ ይጠበቅ ከነበረው የደሞዝ ጭማሪ በታች እንደ ጨመረ ብዙዎች ይስማማሉ፡ ፡ በሰላሳና አርባ ፐርሰንት ብቻ የሚወሰን ጭማሪ ያደርጋል ብሎ ላለመገመት ታላቁ መነሻ መንግስት ቀድሞ ይሰጣቸው የነበሩ የሚያጓጉ መግለጫዎች ነበሩ፡፡የሆነው ሆኖ፣ ሀገራችን ይህን በመሰለ የወል እውነታ ውስጥ እንዳለች እየታወቀ፣ የኑሮ ውድነት ከእለት እለት ሲባባስ፣ አሁንም መፍሄ እየተባሉ የሚወሰዱ እርምጃዎች ችግር ሲያባብሱ እንጅ ሲያሻሽሉ እያየን አይደለም፡፡
ሰሞኑ የተጨመረው የደምዝ ጭማሪ ውጤታማ እና አመርቂ አለመሆኑን በሰራ ላይ እናየዋለን ለምሳሌ ያክል ስኳር አቅርቦትን መንግስት አገር ውስጥ የሚያደርሳቸውን ምርት ለህብረተሰቡ በበቂ ከማዳረስ ያለፍ ገበያውን በማን አለብኝነት ተቆጣጥሮ ድሃውን ህዝብ የዕለት ጉርሱን በመንጠቅ ለረሃብ እና እርዛት ዳርጎታል።ታሪክ
እንደሚያወሳው ከሆነ በንጉሱ ዘመን የመጨረሻ ስርዓት መውደቅ ለፊውዳሉ የቀረቡና የንጉሱን ቤተሰቦች ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ስልጣን ላይ መቀመጥ መሞከር ትልቁ ምክንያት በትራንስፖርት ላይ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በአገሪቱ ላይ በመደረጉ ነበር።የኢህአዴግ መንግስት ስልጣን በተረከበ ዘመን ኢኮኖሚውን በምኒተሪ እና በፊሲካሊ ፖሊሲ በነፃ የንግድ ስም ህዝቡን እያታለሉ በማደናገር የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም የሚደረግ ስልታዊ መንገድ ነው።
በአገራችን የምትገኝበት ከፍተኛ የሆነ የኑሮ ምስቅልቅል፣የፖለቲካው ነፀብራቅ ነው።የዚህ ምስቅልቅል በመሆኑም ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው አንዱ ማሳያ ከፍተኛ የሆነ የዜጎች ስደት ነው።ባለፉት ዓመታት በኢኮኖሚው እና ፖለቲካው ዙሪያው ባጠኑት ጥናት ተቋማት የኢትዮጵያ ዜጎቿ ለኑሮ የማይመርጧት ሀገር እንደሆነች ተዘግቧል። 46% የሚቆጠሩ ዜጎች ከሀገራቸው ውጭ በስደት የመከራን ሕይወት ለመግፋት ተገደዋል።ዜጎች ባገራቸው ሰርቶ የመኖር ዕድሉን ማግኘት ካልቻሉበት ሀገር፣ስደት መምረጣቸው ፣የትምህርት፣የስራ ፣የቁጠባ ዕድል ለሁሉም እንዲደርስ ማድረግ ግድ የሚል በተለይ ወደ ዓረብ አገራት የሚሄዱ እህቶቻችን የሚደርስባቸው ግፍና ውርደት ፣ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ነው።ሁሉም አንገት የሚያስደፋ ሆኖዋል።በነዚህ ሀገሮች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሰሩበትን የደመወዝ ይከለከላሉ፣ ዜጎች በቂ ጥሪት እንዲያፈሩ ከማገዝ ጎን ለጎን ይደበደባሉ፤ ይደፈራሉ፤ በግፍ ይታሰራሉ፤ አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ይገደላሉ፡፡ ይህ ዓይነት የዜጎች መብት በድርጅት፣በማህበረሰብን ጥቅም መብት ማስከበር አልቻለም።በኢትዮጵያ የተከሰተው የኑሮ ውድነት ዘላቂ መፍትሔ ያገኝ ዘንድ ሕዝቡ በመንግስት ላይ ግፊት ማድረግ አለበት።በምርጫ ሰምን የሚደረግ የደመወዝ ጭማሪ ማስተካከያ ህዝብን መደለል አይቻልም።ቸር እንሰንብት፡፡

Monday, August 18, 2014

እንደገና ይድረስ ለሠራቱ



“የትግሬ” ነፃ አውጪ ነኝ ብሎ ራሱን የሠየመው የዘረኞችና የዘራፊዎች ቡድን አገሪቷን እያጎሳቆለ ያለው ከሠራዊቱ ጀርባ ተንጠላጥሎ መሆኑ ይታወቃል። ይህ የዘረኞችና የዘራፊዎች ቡድን የተሸከመውን ሠራዊት ሳይቀር በጉስቁልናና በድንቁርና እንዲኖር ፈርዶበታል። ህወሃት ሠራዊቱ እንዲማር፤ ዘመኑ ከሚፈቅደው የቴክኖሎጂ እውቀት ጋር ራሱን እንዲያዋህድ እና በራሱ የሚተማመን የዘመነ ሠራዊት እንዲሆን ፍላጎት የለውም።አሜሪካን በአገሯ በሚገኙ የጦር ትምህርት ተቋማት ውስጥ ወታዶሮችን ለማሰልጠን ፍላጎት ብታሳይም ሳሞራ የኑስና መለስ ዜናዊ እምቢ ማለታቸውን አብዛኛው የሠራዊቱ አባላት የሰሙት አይመስልም። አሜሪካን በሁለት ዓመት ውስጥ ብቻ 42 ወታደሮችን አገሯ ወስዳ ለማስለጠን በጠየቀች ግዜ ሳሞራ የፈቀደው 13 ወታደሮች ብቻ ሂደው እንዲማሩ ነው። እነዚህም ከህወሃቶች መካከል ፊደል የቆጠሩ ተፈልገው በመገኘታቸው መሆኑም ታውቋል። በሠራዊቱ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች የትምህርት ዝግጅት ቢኖራቸውም የትምህርት እድሉን ተከልክለዋል።
ህወሃት ከራሱ ውጪ ያሉት ሌሎች ላይ ምንም ዕምነት እንደሌለው በተለያየ አጋጣሚ ተናግሮታል። የትምህርት ዕድሉን ለምን መጠቀም እንዳልፈለጉ ሲጠየቅ ሳሞራ የኑስ “ሌሎችን አናምናቸውም አሜሪካን ሂደው ይቀራሉ” ብሎ መልስ መስጠቱም ተመዝግቦ ይገኛል። 11ኛ ክፍልን ያልዘለለው የህወሃቱ ኢታማዦር ሹም ሳሞራ የኑስ ሠራዊቱን ታማኝና የማይታመኑ በሚል ይከፍላቸዋል። የህወሃት አባል የሆነ ወታደር ታማኝ ፤ ሌሎች የሠራዊቱ አባላት የማይታመኑ።
አሁንም የሠራዊቱ አባላት ስሙ !
እናንተ ምንም ያክል ጥሩ ዜጋ ለመሆን ብትጥሩ በህወሃቶች ዘንድ የምትታመኑ አይደላችሁም። ህወሃቶች ከእነርሱ ውጪ ባሉ ሌሎች ላይ ጥርሳቸውን እንደነከሱ እስከ ዛሬ አሉ። በሌሎች ዜጎች ላይ የመዘዙት የበቀል ሰይፍም ወደ ሰገባው የሚመለስ አልሆነም። በሁለት ዓመት ውስጥ 42 ወታደሮችን አሜሪካን ወደ አገሯ ወስዳ ለማስልጠን ብትጠይቅም 13ቱን ብቻ ተቀብለው 29ኙን አንፈልግም ማለታቸው የተመዘዘው የበቀል ሰይፋቸው አንዱ አንጓ መሆኑን የትምህርት ዕድሉን የተነፈገው የሠራዊቱ አባል ልብ ሊለው ይገባል። እነ ሳሞራ የኑስ ከእነርሱ ውጪ ያሉ ሌሎች ዜጎች በድንቁርናና በችጋር እየተሰቃዩ ይኖሩ ዘንድ ፈርደውበታል። በእንዲህ ሁኔታ እንዲኖር የተፈረደበት ሠራዊት፤ ውጪ አገር ሂዶ እንዳይማር የተከለከለ ሠራዊት፤ ዘር ሃረጉ እና ድርጅታዊ ታማኝነቱ እየታየ ለሹመት የሚበቃው የሠራዊት አባል ይህን ውስኔ ለወሰነበት ለመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን ከሚያገኛት ከወር ደመወዙ ላይ ቆርጦ እንዲከፍል ይደረጋል። እንዲህ ዓይነት በደል በየትኛውም አገር ታይቶ አይታወቅም።
በችጋር እንድትኖሩ ከምታገኟት ከወር ደመወዝችሁ ላይ ይወሰዳል፤ ተምራችሁ ራሳችሁን እንዳትቀይሩ በነፃ የሚገኘውን የትምህርት ዕድል እንኳ እንዳትጠቀሙ ተከልክላችኋል። በዚህ ሁኔታ እንድትኖሩ ከተፈረደባችሁ በኋላ የገዛ ወገኖቻችሁን ደም በከንቱ እንድታፈሱ ትደረጋላችሁ። የቀደመው ትውልድ በደሙ ያቆመው ድንበር ፈርሶ እና ዜጎች ተፈናቅለው መሬቱ ለባዕድ ሲሰጥ አናንተ ቁማችሁ ትመለከታላችሁ። ያ የሚፈሰው ደም የራሳችሁ ደም፤ ተፈናቅሎ ሜዳ ላይ የሚወድቀው የገዛ ወገናችሁ መሆኑን ለማሰብ እንኳ ነፃነት ያጣችሁ ትመስላላችሁ። የህፃን ደም በአዲስ አበባ ጎዳና ላይ ሲፈስ ለምን ስትሉ አልተሰማም፤ ጋምቤላዎች ለዘለዓለም ከኖሩበት መሬት ተፈናቅለው መሬታቸውን ሌሎች ሲቀራመቱት ይሄ አይሆንም ለማለት የያዛችሁት ነፍጥ የሸንበቆ ምርኩዝ ሁኖባችኋል። በኦጋዴን ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል ሲፈፀም ተባባሪ ትሆናላችሁ። ህወሃቶች በዚያች አገር ለሚፈፅሙት ማንኛውም ወንጀል እናንተ የእነርሱ በትር ሁናችሁ ታገለግላላችሁ። ከዚያች አገር ከሚገኘው ሃብት ግን ተካፋይ አትሆኑም። እነርሱ ሚሊየነር ሁነው የሚያደርጉትን ሲያጡ፤ አናንተ የሠራዊቱ አባላት ግን በችጋር ከነ-ቤተሰቦቻችሁ ትሰቃያላችሁ። ይሄ ሁኔታ ማብቃት የኖርበታል።
የአገሪቷ መከላከያ ኃይል ራዕይ ተብሎ የተነገረህ እንዲህ ይላል “. . . ለህገ-መንግስቱ እና ለህዝቡ ፍፁም ታማኝ የሆነ . . . የሃገራችን ህዝቦች ተምሳሊት የሆነ . . . የእውቀት መፍለቂያ የሆነ ሠራዊት መገንባት “
ምንም እንኳ ጥሩ ራዕይ ተቀርፆ የተቀመጠ ቢሆንም አንተ የሠራዊቱ አባል ግን የዚህ ራዕይ ተካፋይ አይደለህም።አንተ የምትካፈልው መከራውን እንጂ መልካሙን ራዕይ አይደለም። ለህገ-መንግስቱ እና ለህዝቡ ፍፁም ታማኝ የሆነ ሠራዊት መገንባት የሚለውን ራዕይ መልሰህ መልሰህ እንድታስብ እንመክርሃለን። በእኛ በኩል ግን ህወሃት በአገሪቷ ጫንቃ ላይ ከተቆናጠጠ ዘመን ጀምሮ ህዝቡን ሲያዋርድ ኖረ እንጂ ለህዝብ ታማኝ ሲሆን አልታየም። ህገ-መንግስት ብሎ ራሱ እዚያ ጫካ ሁኖ የፃፈውን ራሱ ሲያፈርሰው ኖረ እንጂ ሲያከብረው አላየንም። ህወሃት ለህገ-ማንግስቱ እና ለህዝቡ ታማኝ ሁኖም አያውቅም። ወደ ፊትም ራሱን ከህዝብ እና ከህግ-በታች አድርጎ እንዳይኖር እሰከ ዛሬ ሲፈፅመው የኖረው ወንጀል የሚያስችለው አይሆንም። ህወሃቶች ከነ እድፋቸው ወደ ማይቀረው መቃብራቸው መሄድን የመረጡ ስለሆነ ሠራዊቱ ራሱን ከእነዚህ ነውረኞች ለይቶ ለህገ-መንግስቱና ለህዝቡ ፍፁም ታማኝ መሆኑን ማስመስከር ይጠበቅበታል።
ሌላው ከህወሃት ውጪ ያላችሁ የሠራዊቱ አባላት ልታስቡበት የሚገባው ዓቢይ ነገር ደግሞ ‘የሃገራችን ህዝቦች ተምሳሊት የሆነ ሠራዊት መገንባት ‘ የሚለውን ራዕይ ነው። ሃገራችን ከ80 በላይ ብሄሮች የሚኖሩባት መሆኑ ይታወቃል።ለዚህች አገር ምሳሌ ሊሆን የሚችል መከላከያ ኃይል መገንባት እንደ ራዕይ የተቀመጠ ቢሆንም በተግባር የሆነው ግን ሌላ ነው። አሁን ባለው የአገሪቷ መከላከያ ኃይል ውስጥ ያሉ የጦር አዛዦችን ቀና ብለህ አይተህ እውነት መከላከያ ሃይሉ የህዝቦቿ ተምሳሊት የሆነ ሠራዊት መሆኑን ራስህ እንድትመልስ እንጠይቅሃለን። በአገሪቷ የተሾሙ ጄኔራሎች ከአንድ ጎጥ እና መንደር የተሰባሰቡ መሆናቸው በምን መልኩ የሃገራችን ህዝቦች ተምሳሊት የሆነ ሠራዊት ሊሆን እንደሚችል ህወሃቶችን ደግሞ ደጋግሞ መጠየቅ ተገቢ ይሆናል።
በመጨረሻም ‘የዕውቀት ምንጭ የሆነ ሠራዊት መገንባት’ የሚል ራዕይም በጉልህ ተፅፎ ተቀምጧል። የህወሃት የጦር አበጋዞች ከ7ኛ ክፍል ያልዘለሉ፤ካርታ ይዘው የቆሙበትን ሥፍራ እንኳ ለማሳየት የሚደናበሩ መሆናቸው የታወቀ ነው። እነዚህ ፊደል ቆጥረው ያልዘለቁ ቡድኖች የሚመሩት ተቋም እንደምን ሁኖ የዕውቀት ምንጭ ሊሆን እንደሚችል የሚያውቅ የለም። የህወሃቶች እውቀት የንፁሃን ደም ማፍሰስ፤ የድሃ ሃብት መዝረፍ፤ እኔ ብቻ ባይነት እንጂ ከዝህ የዘለለ ሌላ እውቀት ያላቸው አይደሉም። እነርሱ ባለመማራቸው የጎደለባቸው ነገር አለመኖሩን እያዩት ለትምህርትና ለተለየ ዕውቀት ዋጋ ይሰጣሉ ማለት አይቻልም። ሌሎቹም ተምረው እውቀት እንዲገበዩ ለማድረግ ስብዕናቸው አይፈቅድላቸውም። በዚህም ምክንያት ከውጭ አገራት በነፃ የሚገኘውን የትምህርት ዕድል እንኳ ወታደሩ ተጠቅሞ ራሱን በእውቀት እንዳያዳብር ይከለክላሉ። እንዳይማር የተከለከል የሠራዊት አባል እንደምን ሁኖ የዕውቀት መፍለቂያ ሊሆን እንደሚችል የሠራዊቱ አባላት የሽፍቶቹን ቡድኖች መጠየቅ ይኖርባችኋል።
የሠራዊቱ አባል የህዝብ አካል መሆንህን አትርሳው። ነገ ዞረህ የምትገባውም እዚያው ከወጣህበት ህዝብ መሆኑን እኛ ልናስታውስህ እንወዳለን። አሁን ባለው አካሄድህ የወጣህበትህን ድንኳን፤ በዚያች ድንኳን ውስጥ ሁነህ ያሳደጉህ ወገኖችህን እያሳደድክ መሆንህን አስታውስ። የወጣህበትንም ድንኳን እያፈረስክ ነው። ድንኳንህንም አፍርሰህ ከጨረስከው ነገ ዞሮ ማረፊያ እንደማይኖርህ ደግሞ እኛ ልናስታውሰህ እንፈልጋለን። ጥሪያችንን መስማት ከማንም በላይ ለራስህ ይበጅሃል። የወገኖችህን ጥሪ ሰምተህ በወገኖችህ ላይ የተመዘዘውን የበቀል ሰይፍ ለማቆም ከህዝብ ጎን መሆንን አልመርጥ ካልክ መጨረሻህ አያምርም። እነ ሳሞራ የኑስ ጠላቶችህ እንጂ ወገኖችህ አይደሉም። እነ ሳሞራ የኑስ አንተንና ልጅ ልጆችህን ጭምር በድንቁርና አዘቅት ውስጥ አኑረው ቀጥቅጠው ለመግዛት ያላቸው ፍላጎት ወሰን እንደሌለው ማወቅ ይኖርብሃል። የተሸከምከው መሣሪያ ለፍትህ ለእኩልነት፤ ለነፃነት እና ለእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እንቅፋት የሚሆኑትን የሚፋለም ሊሆን ይገባዋል እንጂ እነዚህን ጥያቄዎች ባነሱ ወገኖች ላይ የሚያነጣጥር መሆን አይኖርበትም።
እንግዲህ ምን እናድርግ እያላችሁ የምትጠይቁን አላችሁ። ለዚህ ጥያቄ መልሱ ያለው ከእናተው ደጅ ነው። እኛ ያነሳነውን ጥያቄ ባላችሁበት ሁናችሁ ማንሳት ትችላላችሁ። አብዛኛው ሠራዊት ጥቂት ዘረኞችንና ዘራፊዎችን ተሸክሞ የሚኖሩበት ሁኔታ ለመቀየር ሦስትም አራትም እየሆናችሁ እምቢ ማለት መጀመር አለባችሁ። ህወሃቶችን ተሸክማችሁ፤ የህዝባችሁ ጠላቶች ሁናችሁ፤ አገራችሁንና ህዝባችሁን አዋርዳችሁ የምትኖሩት ኑሮ ኑሮ አይደለምና እምቢ አይሆንም ማለት ጀምሩ። ለዘረኞቹና ለዘራፊዎቹ ህወሃቶች ከመሞት ይልቅ ለፍትህ፤ ለእኩልነት እና ለነፃነት ብላችሁ ብትሠው መሥዋእትነታችሁ ለዘላለም ሲዘከር ይኖራል፤ ስማችሁም ከመቃብር በላይ ይሆናል።ፍፃሜያችሁም የጀግና ፍፃሜ ይሆናል።
ፍፃሜያችሁ የጀግና ፍፃሜ እንዲሆን ለፍትህ፤ ለነፃነት እና ለእኩልነት ዘብ የምትቆሙ ሁኑ እንጂ የአንድን ዘረኛና ዘራፊ ቡድን እድሜ ለማራዘም የምትቆሙ አትሁኑ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

Students with no gov’t policy, strategy training to be denied College entry

Students with no gov’t policy, strategy training to be denied College entry

Students with no gov’t policy, strategy training to be denied College entry

ESAT News

 The Ethiopian Ministry of Education has issued a mandatory directive that compels over 350 thousand new and existing university students to be trained in government’s policy and strategy. The directive also states that students who do not hold the certificate of completion cannot continue their studies.
The Minister, Shiferaw Shigute said to journalists that the 116,000 new and 250,000 existing students will be given the training for 15 days receiving per dime. The first round of the training starts next week while the second one will be given in September next year.
He said the trainers will be senior government officials but refused to reveal the details and the cost of the training. Other sources however said some of the course modules include Developmental State, Religious Extremism and Terrorism. The ruling Front is doing this in order to get support in next year’s election and succeed its members with university students. The source also revealed that the finance comes from the government’s coffers.
Similarly, a training is being given to Federal judges, prosecutors, police and security officers about the ruling Front’s ideology, Revolutionary Democracy. Training participants have asked about the need for the training at this time and if judges can act freely when they are being trained by ruling party officials about its policies.
Questions were also raised about the potential of future unilinguality in Ethiopia, Emperor Menelik’s legacies and government’s growth rhetoric. Answering to the questions, Front’s official, Abadula Gemeda, said during Menelik’s reign there was “class subjugation in the Amhara region while there was ethnic subjugation in Oromia region”. He also said his Front follows Taiwan’s and India’s developmental state ideologies.
The ruling Front is holding discussions and training with top officials, civil servants and public representative cadres about current national issues.

አቶ ብርሃኑ በርሀ የዓረና ትግራይ ፓርቲ ሊቀ መንበር በወቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ላይ ለ ሎሚ መፅሄት የሰጡት ቃለ መጠይቅ

አቶ ብርሃኑ በርሀ የዓረና ትግራይ ፓርቲ ሊቀ መንበር በወቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ላይ ለ ሎሚ መፅሄት የሰጡት ቃለ መጠይቅ

አቶ ብርሃኑ በርሀ የዓረና ትግራይ ፓርቲ ሊቀ መንበርAugest 18/2014
ሎሚ* ለመሆኑ አሁን ፓርቲያችሁ በምን አይነት ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል?


አቶ ብርሃኑ:- ፓርቲያችን ዓረና ትግራይ የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች የፓቲርው ጠቅላላ ጉባኤ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ተግባራዊ ማድረግ መሰረት ያደረገ ሆኖ ጠቅለል ብሎ ሲገለፅ የዓረና አማራጭ ፖሊሲና በወቅታዊ ሃገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ያለው አ ም ለህዝብ በማስተዋወቅ የአረና አማራጭ ፖሊሲዊች የህዝቡ አጀንዳና የፍላጎቱ መገለጫ ሆነው ከፓርቲ ፖለቲካ ወደ የህዝብ ፖለቲካ በማሸጋገር የነፃና ፍትሃዊ ምርጫ እድል ተፈፃሚነት በህዝቡ የነቃ ተሳትፎ ዋስትና እንዲያገኝ ለማስቻል ተከታታይ የህዝብ ፖለቲካዊ ስብሰባዎች ማካሄድ ፣ አማራጭ ፖሊሲያችን በማስተዋወቅ የምንፈጥረው ተቀባይነትና ድጋፍ የፈጠረልን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ፓርቲያችን በአባላትና በደጋፊዎች ብዛት እንዲሁም በአደረጃጀት መዋቅራችን በማስፋት እራሳችንን ለሰላማዊ ፣ሕጋዊና ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ውድድር ብቁ ሆኖ መገኘትን ያለመ ነው ፡፣ የዓረና አማራጭ ፖሊሲ የህዝቡ አጀንዳ ሆኖ ህዝቡ ይጠቅመ’ል የሚል ግንዛቤ ወስዶ የራሱ አጀንዳ አድርጎት ለውጤታማነቱም ወሳኙ ራሱ ህዝብ መሆኑን እንዲገነዘብና ያን ለማድረግ ህዝብ ብቃቱም ችሎታውም እንዳለው እንዲገነዘብ ማስቻል የፖለቲካ ስራችን አቅጣጫና የሰላማዊ ትግላችን ስትራተጂ መመርያም በተግባር ለመፈፀም ነው የምንንቀሳቀሰው፣፣

 ሎሚ* ዘመቻ አብርሃ ደስታ ብላችሁ ያዘጋጃችሁት ፕሮግራም እንዴት ነበር?  

አቶ ብርሃኑ:- አብርሃ ደስታ ሀገራዊ ራኢ ከሰነቁና የአረና አመራር ወራሾች ይሆናሉ ተብለው ከምንገምታቸው ንቁ የአረና ወጣት አመራሮች አንዱ ነበር፡፣ አካዳሚያዊና ፖለቲካዊ ብቃቱ ተስፋ የሚጣልበት መሆኑን በተግባር አሳይቶአል ፣ ለማነበት ራኢ ግብራዊነት የማይታጠፍ የፀና አ ም አሳይቶአል ፣ አጠቃላይ ፖለቲካዊ ስብእናውና የመቀስቀስ ችሎታው የሚደነቅ ነው፣ የኤሌክትሮኒክስ ቴክኒዮሎጂ በመጠቀም የፌስቡክ ንጉስ እስኪመስል ሰርቶአል ፣ አስተምሮአል አሳምኖአል ተደናቂነትም አትርፎአል፣ ይህ በመሆኑ ለአብርሃ ደስታ ብቻ ሳይሆን ውለታና ምስጋና ለሚገባቸው ወጣት መሪዎች ክብርና አድናቆታችን ለመግለፅ ከመታሰሩ በፊት ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ እንዲካሄድባቸው አብሮን ውሳኔ የሰጠባቸው የራያ አዘቦ ወረዳ አከባቢ ያካሄድነው ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ ዘመቻ አብርሃ ደስታ ብለናቸዋል ፣
[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

የወያኔው ኢንሳ በአዲስ መልክ የፌስቡክ ስም አጥፊ ፔጆችን/ገጾችን ሊያደራጅ ነው

የወያኔው ኢንሳ በአዲስ መልክ የፌስቡክ ስም አጥፊ ፔጆችን/ገጾች

ን ሊያደራጅ ነውAugust 18/2014

=================ነቢል አህመድ ዘገፈርሳ=====================
facebookወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት እና ነጻነት ለመሸራረፍ ብሎም ለመበታተን ከሚጠቀምባቸው ዘዴዎች አንዱ በማህበራዊ ድህረገጹ ያሰማራቸውን ከተቃዋሚ ሃይላት ጋር ተመሳስለው የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት መስለው የተቃዋሚ ሃይሎችን ሎግ በመጠቀም እንዲሁም ለሽፋንነት በየመሃሉ የተቃዋሚ ድርጅቶችን መግለጫ እንደወሽመጥ በማስገባት በማታለል እና በማጭበርበር ላይ ተመስርተው ሲሰሩ የነበሩ ስም አጥፊ ገጾችን/ ፔጆችን በአዲስ መልክ ለማደራጀት በዚህ ሳምንት እረፍት እንዲወስዱ ያደረጋቸው መሆኑ ታውቋል።
ስም በማጥፋት ለውጥ ፈላጊ ሃይሎች በተለያዩ አክቲቪስቶች ላይ መጠራጠር እንዲያሳድሩ እና ጠቃሚ የተባሉ ጦማርያንን እንዲያጡ እና ትግሉ አቅጣጫውን እንዲስት በስፋት አዲስ የአሰራር ዘይቤ ለመቀየስ የተሳዳቢዎች የተዛልፊዎች እና የስም አጥፊዎች የማህበራዊ አካውንት እና ፔጆች እረፍት ላይ መሆናቸውን እና በተጠናከረ መልኩ ወደ ስራ እንደሚመለሱ በቅርብ የሚያውቋቸው ወዳጆቻቸው ተናግረዋል።
በዚሁም መሰረት በዜጎች መካከል ከባድ ጥርጣሬን ያጭራሉ የተባሉ የፈጠራ ጽሁፎች እና የሞቱ ሰዎች ፎቶዎችን በመጠቀም የተለያዩ የፌክ ወንጀሎችን በመጻፍ እንድሁም ከብልግና እና የሰውን ክብር ከሚያዋርዱ አዳዲስ ብካይ የሃሰት መረጃዎች ጋር ወዘተ ተያይዘው ወደ ማህበራዊ ድህረገጾች እርፍታቸውን ጨርሰው እንደሚመጡ ታውቋል።

Sunday, August 10, 2014

‹‹አያ ጅቦ ሳታመኻኝ ብላኝ›› በበፍቃዱ ሃይሉ (ከእስር ቤት የተላከ ማስታወሻ)


August 10, 2014       
‹‹ታዲያ ጥፋቴ ምንድን ነው ትላለህ?!››፣ ብሎኛል አንዱ መርማሪዬ ስለዞን ዘጠኝ እና እኔም እራሴ እንደጦማሪም እንደአራማጅ ተራማጅም ሠራሁ የምላቸውን ነገሮች ዝርዝር ነግሬው ሳበቃ፡፡ በኋላ ላይ በእስር ቤት ቋንቋ ከ‹‹አባሪዎቼ›› ጋር መገናኘት ከተፈቀደልን በኋላ ስንጠያየቅ  ለካስ ሁላችንም ይቺኑ ጥያቄ ተጠይቀናል፡፡ ይኼ ነው እንግዲህ የምርመራችንን ሒደት የሚገልፀው ጥያቄ፡፡ ‹‹ተጠርጥረን›› የተያዝንበትን ጉዳይ የሚያረጋግጥ ሥራ ሠርተን ባለመገኘታችን (ወይም ‹‹ባለመናገራችን››) ታዲያ ጥፋትህ ምንድን ነው? ተባልን፡፡ ምርመራው የኛን ነፃ መሆን አለመሆን ለማጣራት ሳይሆን ጥፋት ለማግኘት ነበር፡፡ ብዙዎች ‹መንግሥት ዞን ዘጠኝን ለምን ሁለት ዓመት እንደታገሠው› ግራ በመጋባት ይጠይቃሉ፤ ባሕሪው አይደለምና፡፡ የኢትዮጵያ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት ምኅዳር በቀላሉ እንደገመቱት ተይዘን፣ ተመርምረንና ‹‹ተገኘባችሁ›› የተባልነው ‹‹ የግንቦት 7 [እና ኦነግም ጭምር] አባልነት [ብሎም ግብ አስፈጻሚነት] ›› በሽታ ለተከሳሽነት አብቅቶናል፡፡ ቀጣዩ የክርክር ሂደት ነው፡፡
Befekadu Hailu
ከዚያ በፊት ግን ዞን ዘጠኝን በሩቅም በቅርብም የሚያውቁ በግራ መጋባት መልስ እንደሚሹ በማሰብ ይቺን አጭር ማስታወሻ ለመጻፍ ተገድጃለሁ፡፡ የእስራችን ሂደት ምን ይመስላል? የምርመራችንስ? እውን የግንቦት ሰባት አባል ነን? [ታዲያ] ለምን ታሰርን? በቅርቡ እንፈታ ይሆን?
ደቂቅም ይሁን ሊቅ ስለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እውነታ የሚጽፍ ማንኛውም ሰው [ኢትዮጵያ ውስጥ ሳለ] አንድ ቀን እታሰር ይሆን እያለ መስጋቱ አይቀርም ፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም በአንድ መጽሐፋቸው ላይ ሰው ነገረኝ ብለው የኢትዮጵያ ሕዝብን በሦስት የመደቡት፡- የታሰረ፣ ታስሮ የተፈታ እና ወደፊት የሚታሰር በማለት፡፡ እርግጥ ዞን ዘጠኝ ‹‹ሐሳቡን መግለጽ ፈርቶ ዝም ያለ ሁሉ እስረኛ ነው›› ብሎ መደምደም ሦስቱም ምድብ አንደኛው ውስጥ ያጠቃልለዋል ‹‹የታሰረ›› በሚል፡፡ ዞን ዘጠኞች ጦማራችንን በከፈተን በሁለት ሳምንት ሲታገድብን እና ሌላ ስንከፍት ግና መጨረሻ ላይ ታጋቾቹ እኛ እንደምንሆን እናውቅ ነበር፡፡ ያንን የሚያረጋግጥ ተደጋጋሚ የደህንነቶች ክትትል እና ምልክቶች ስለደረሱን መታሰራችን ማስደንገጡ ባይቀርም ያልተጠበቀ ግን አልነበረም፡፡
እስሩ በክትትሉ የተገኘነውን ስድስት የዞን ዘጠኝ አባላት እና ሦስት ጋዜጠኛ ጓደኞቻችንን መሆኑን በተለይ የጋዜጠኞቹ [ቢያንስ ለእኛ] ያልተጠበቀ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ የኋላ ኋላ ስንመለከተው ግን በእኛ አስታኮ እነሱንም ማሰሩ የታሰበበት ዘመቻ እንደሆነ መገመት አይከብድም፡፡ እኛን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሒደትም ቢሆን በቅጡ የታሰበበት ነበር ሁላችንም (ከአስማማው በቀር) ከቀኑ በ11፡00 ገደማ በያለንበት ስንያዝ አስማማው በማግሥቱ ታስሯል፡፡  ሌሎቻችን ቤታችን በሚፈተሸበት ሰዓት ሕጉ የሚፈቅድበት ሰዓት(12፡00) አልፎ ነበር፡፡ በቁጥጥር ስር ካዋሉን በኋላ የሕገ-ወጥ አያያዝ ሰለባ የመሆናችን ሂደት የሚጀምረው ከዚህ ነው፡፡
ማዕከላዊን በክፉ ስሙ ቀድሞ ለሚያውቀው ሰው ግቢውን መርገጥ በራሱ ልብን ያርዳል፡፡ ሆኖም በልቤ /ጓደኞቼም እንደእኔ ሳይሰማቸው አይቀርም/ አንደኛ እኛ ጸሐፊ እንጂ ወታደር ወይም ሰላይ ባለመሆናች፣ ሁለተኛ መቼም ከበፊቱ የተሻለ ሰብዓዊ አያያዝ ሳይኖርም አይቀርም የሚል የዋህ ተስፋ በማሳደሬ ብዙም አልተሸበርኩም ነበር፡፡ የገባሁ እለት ከታሳሪዎች በተሰጠኝ ማብራሪያ ‹‹ሳይቤሪያ›› መግባቴን አወቅኩ፡፡ ከዚያ የ HRW-They want confession የተሰኘ ሪፖርት ላይ የተፃፉ ነገሮች ሁሉ ትክክል መሆናቸውን ለመረዳት የፈጀብኝ ከአንድ ሳምንት ያነሰ ጊዜ ነበር፡፡
ምርመራ ማዕከላዊ ስታይል
ምርመራ በማዕከላዊ ከብልጠት ይልቅ ጉልበት ይበዛበታል፡፡ መርማሪዎቹ የምርመራ ችሎታቸው ተጠርጣሪውን የተጠረጠረበትን ጉዳይ ከማውጣጣት ይልቅ የምርመራ ችሎታ እንዳላቸው ለማሳመን የሚጥሩበት ጊዜ ይበዛል፡፡ ይህም አልሰራ ሲል ጥፊ፣ ካልቾ፣ ከአቅም በላይ ስፖርት ማሰራት እና ግርፋት ድረስ ይዘልቃሉ፡፡ ይህ እንግዲህ እኔ ላይ ከተፈራረቁብኝ አምስት መርማሪዎች እና ሌሎችም አብሮ ታሳሪዎቼ ከነገሩኝ የተረዳሁት ነው፡፡ እርግጥ ሌሎች ‹‹እርቃንን ቁጭ ብድግ›› የሰሩ ተጠርጣሪዎችም ገጥመውኛል፡፡ ከባባድ ቅጣት (ወፌ ላላ ግርፋት፣ ጥፍር መንቀል) የደረሰባቸው ሌሎች ታሳሪዎች አብረውኝ የታሰሩ ቢሆንም ይህ የተፈፀመባቸው ግን ወደማዕከላዊ ከመምጣታቸው በፊት  ነው፡፡ ከነዚህ መካከል የሀሮማያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ይገኙበታል፡፡ የሚገርመው በዚህ ዓይነቱ ምርመራ የሰጡት ቃል ለማመሳከርያ ማዕከላዊ መምጣቱ ነው፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ወደማዕከላዊ ከመዛወራቸው በፊት ከባድ ቅጣት የተቀጡበትን ቦታ የት እንደሆነ እንዳያውቁ አይናቸው ተሸፍኖ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እሥረኞችም መኖራቸው ነው – የደርግን ‹‹ቤርሙዳ›› ያስታውሳል!
እናም በሚያዋርድ እና ክብርን በሚነካ ስድብ በሚያስፈራ የቤቱ (የማዕከላዊ) ጥላ እና ኃይል በተቀላቀለበት የምርመራ ሂደት የተከሳሽ ቃላችንን ሰጠን፡፡ ቃላችን መቶ በመቶ እውነት አልነበረም፡፡ ጫናው በበረታ ቁጥር መስማት የሚፈልጉትን ‹‹ዓመፅ ለመቀስቀስ ፈልገን›› የመሳሰሉ በራስ ላይ ፈራጅ (Self-incriminating) ሐረጎችን እየተናገርን ነበር፡፡ ያም ግን ለመርማሪዎቻችን በቂ አልነበረም፡፡ ስለዚህ በሚጽፉበት ሰዓት እያንዳንዷን ‹‹ሠራን›› ያልነውን ሁሉ ሊያስከስሰን በሚችልበት ሁኔታ እየገለበጡ እና እየበጠበጡ ፃፉት፡፡ አንዳንዶቻችን እየተከራከርን ሲያቅተን ፍርድ ቤት ይፍታው ብለን ፈረምን፣ቀሪዎቻችን የቻልነውን ያህል ተደብድበንበት ፈረምን፡፡ ‹‹ከተናገርኩት ቃል ውጪ አንድም ቃል አልፈርምም›› በሚል እስከመጨረሻው ታግሎ የተሳካለት አቤል ብቻ ነበር፡፡
በምርመራው ሂደት የተረዳነው ነገር ቢኖር የማዕከላዊ መርማሪዎች ብቃት (Intelligence) አርጩሜ ብቻ መሆኑን ነው፡፡ እኔ ምርመራ ሲባል ይመስለኝ የነበረው ፖሊሶች ተጠርጣሪዎችን ፈፀሙ ስለሚባለው ነገር በቂ መረጃ ይዘው ግፋ ቢል ለምንና እንዴት እንደፈፀሙት ማውጣጣት ነበር፡፡ ‹‹ዕድሜ ለማዕከላዊ›› የተረዳሁት ነገር ቢኖር ምርመራ ማለት ለካስ ‹‹የሠራኸው ወንጀል ምንድን ነው?አውጣት!›› ማለት ኖሯል- ማዕከላዊ ስታይል፡፡ ‹‹ነጻ ነኝ›› ቢሉ ሰሚ የለም፡፡ አንዴ ታስረሃል ወንጀል ሊገኝብህ የግድ ነው፤ ካልሆነ ይጋገርብሃል፡፡
አሁን ሳስበው ማዕከላዊ ፈርሶ በሥር-ነቀል ለውጥ እንደገና መቋቋም ያለበት ተቋም ነው፤ ቢያንስ በሁለት ምክንያት፡፡ አንደኛ የምርመራው ሂደት (በራሳችን ጉዳይ እንደተረዳሁት) ትዕዛዝ አስፈፃሚነት ይስተዋልበታል፡፡ ማለትም በመርህ የሚመራ አይደለም፡፡ ሁለተኛ ምርመራው እውቀት መር አይደለም፡፡ ይህ ደግሞ የአገሪቱን ደህንት አደጋ ውስጥ የሚጥል ጉዳይ በምርመራው ድክመት ሳይታወቅ ሊታለፍ ይችላል፡፡ ይህ ችግር የተከሰተው ደግሞ መርማሪ ፖሊሶቹ ከብቃት ይልቅ ለታዛዥነት የተመቹ ታማኞች ሆነው በመመልመላቸው ነው፡፡
‹‹ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ››
በምርመራው ሂደት የተጨቀጨቅነውም ሆነ ተገድደን የፈረምነው ጽሑፎቻችንን የበይነ መረብ ዘመቻዎቻችንን፣ የወሰድናቸው ስልጠናዎችም ሆኑ አንዳንዶቻችን የሰጠናቸው ስልጠናዎች አመፅ ለማስነሳት መሆኑን ‹‹እመኑ›› በሚል ስለነበር የጠበቅነው ግፋ ቢል በወንጀለኛ መቅጫው አንቀጽ 238 ወይም 257 ሊከሱን አስበው ነው ብለን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የክስ መዝገቡ ሲመጣ ‹‹ሽብር›› ያውም ከአስራ አምሰት ዓመት እስከ እድሜ ልክ የሚያስቀጣ አንቀጽ 4 መሆኑን ሳውቅ በበኩሌ ሳቄ ነበር የመጣው፡፡
ማስረጃ ተብለው ከክስ መዝገቡ ጋር የተያያዙት በአብዛኛው ጽሑፎቻችን፣ የዘመቻዎቻችን፣ የጋዜጣ መግለጫዎች እና በተለያዩ ሥልጠናዎች ወቅት የተዘጋጁ የሥልጠና መመሪያዎች (Manuals) ናቸው፡፡ ከዚህ በተረፈ ከግንቦት 7 እና ከኦነግ ጋር ያገናኛችኋል የተባልነው በሦስት ‹‹ሰነዶች›› ነው፡፡ አንደኛው ናትናኤል ኢሜይል ውስጥ በጥቅምት 2001 ተልኮለት የተገኘ የግንቦት 7 የዜና መጽሔት ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ገና የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ አዋጁ ሳይወጣ፤ ግንቦት ሰባትም አሸባሪ ከመባሉ በፊት መሆኑ ነው፡፡ ሁለተኛ ሶልያና ቤት ተገኘ ተብሎ እናቷ ‹‹ቤቴ ውስጥ አልተገኘም፣አልፈርምበትም›› ያሉት እና ለግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ሰራዊት ምልመላ መመዘኛ ሰነድ ነው፡፡ ይህ የሶሊ የዘለቀ አቋም ለሚያውቅ ሙግት አያስፈልገውም፡፡ እኔ እንደውም ትዝ ያለኝ ከመታሰሬ በፊት የትዊተር ፕሮፋይሏ ውስጥ የነበረው ‹‹no for war›› የሚል መፈክር ነው፡፡ ሦስትኛው ደግሞ ማሕሌት ኮምፒውተር ውስጥ የተገኘው የኦነግ ፕሮግራም ነው፡፡ በርግጥ አብረው የተገኙት የሌሎች የኦሮሞ ፓርቲዎች ፕሮግራሞች ማስረጃ ተብለው አለመቅረባቸው መረዳት ብቻ – እሷም ለምን ፕሮግራሙን እንደያዘችው፤ እነሱም ለምን የኦነግን እንደመረጡ ያጋልጣልና የእመኑኝ ሙግት አያስፈልገንም፡፡ በመሰረቱ ሦስቱንም ‹‹ሰነዶች›› መያዝ ከቡድኞቹ ጋር ግንኙነት መመሥረት የሚሰሩትንም መውደድ ማለት አየደለም፡፡ ይህም ለመሪዎቻችን ባይታያቸውም እንኳ ለወገኖቻችን የጠፋቸዋል ብዬ አላስብም፡፡
ሌላውና በአስቂኝለቱ ተወዳዳሪነት የሌለው ውንጀላ ‹‹48 ሺሕ ብር በናትናኤል በኩል ተቀብለው ተከፋፍለዋል›› የሚለው ነው፡፡ ይህ ብር ፤‹‹አሸባሪ›› ከተባሉት ቡድኖች የተወሰደ እንዲመስል በሚያደናግር አገላለጽ የተጻፈ ቢሆንም የክስ መዝገቡ ውስጥ የተያያዘውና ገንዘቡ የመጣበት ደረሰኝ እንደሚያረጋግጠው የተላከው ከARTICLE 19 ነው፡፡ ይህንን ጨምሮ በእስር ላይ ለምትገኝ ጋዜጠኛ ቤተሰቦች መደገፊያ /ለእስረኛይቱም ማበረታቻ/ የተላከ መሆኑን ለመርማሪዎቹ በዝርዝር አስረድተናቸዋል፡፡ ይህንን እያወቁ ውንጀላውን ማኖራቸው እውነትም እኒህ ሰዎች ወንጀለኞች ናቸው ብለው አምነው ሳይሆን ‹‹ከቻልን አደናግረን እናስቀጣቸዋለን (የማይችሉበት ሁኔታ አይታየኝም)፣ካልቻልን ደግሞ በቀጠሮ ጊዜ እንገዛበታለን፣ ነጻ እስኪወጡም ቢሆን በእስር እናቆያቸዋለን›› የሚል ክፉ ምኞት ነው፡፡
… ሳታመኻኝ ብላኝ!
አህዩት ከታች አያ ጅቦ ከላይ ሆነው ወራጅ ውሀ እየጠጡ ነበር አሉ፡፡ ነገር ያማረው አህዩትን ‹‹አታደፍርሽብኝ›› ሲላት ነገሩ የገባት አህይትም ‹‹ሳታመኸኝ ብላኝ›› አለችው ይባላል፡፡ የኛም ነገር እንደዚያው ነው፡፡
ፖሊስ ሲይዘን እኛ ላይ ይህ ነው የሚባል የመክሰሻ መረጃ አልነበረውም፤ እንዲያውም ከስማችን በቀር የሚያውቁት ነገር አልነበረም፡፡ ሌላው ቀርቶ ከደህንነቶታቸው በአንዱ ልከንላቸው የነበረውን የጽሑፋችንን ስብስብ እንኳን ሳያነቡት ነበር የያዙን፡፡
አሁንም ማስረጃ ብለው ከክስ መዝገባችን ጋር ያያያዙት ቢያንስ በእኔ ግምት ዘጠና በመቶ የሚሆነው ‹‹ሰነድ›› እኛው ነፃ ያወጣናል ብለን የሰጠናቸው ጽሑፎቻችን ናቸው፡፡ በመርማሪዎቻችን ንግግር ውስጥ እኛ ላይ ወንጀል የማግኘት Desperate ፍላጎት አይተናል፡፡ ምናልባትም እንደገመትነው ቢያንስ እስከ 2007ቱ ምርጫ ድረስ ከማኅበራዊ ሚዲያ ገለል እንድንልላቸው ፈልገዋል፡፡ ከዚህ የተሻለም አማራጭ አልታያቸውም ይሆናል፡፡
በእስካሁኑ ሂደት የማዕከላዊን ለገዢው ፓርቲ ወገንተኝነት በዓይናችን አይተን አረጋግጠናል፡፡ ቀጣዩ ደግሞ የፍትሕ ሥርዓቱን በአደባባይ መፈተሽ ይቀረናል፡፡ ለአሁኑ ግን በቅርቡ እንፈታ ይሆን… የሚል ጥያቄ ‹ሕጋዊ› ሳይሆን መላ ምታዊ አማራጮችን እገምታለሁ፡፡
ኢህአዴግ ወይም የኢህአዴግ መንግሥት የሚያዘው ፖሊስ እኛን በቁጥጥር ሥር ሲያውለን ስለወንጀላችን ማረጋገጫ (ጠበቆች Beyond reasonable doubt) እንደሚሉት ዓይነት ባይኖረውም መቼም የሆነች ስህተት ሳላገኝባቸው አልቀርም በሚል ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ወትሮም የተንቦረቀቀ የሚባለው የፀረ-ሸብርተኝነቱ አዋጅ ውስጥ የሚጥለን ነገር በቀላሉ ማግኘት አልቻሉም፡፡ አለመቻላቸው ግን የተነሱበትን እኛን የመክሰስ ዓላማ አላጠፋውም፡፡  የክስ መዝገቡን ሲያዘጋጁ አንድም የረባ ዐረፍተ ነገር ሳይጽፉ ይዘውን ፍርድ ቤት መቅረባቸው በራሱ አንድም የረባ ጥርጣሬና ማረጋገጫ እንደሌላቸው አመላካች ነው፡፡ ቢሆንም በቅርቡ ይለቁናል የሚል ግምት የለኝም፡፡ ለምን?
1ኛ. ኢህአዴግ በጣም የሚናደድባቸው እና ታሳሪውን በሚያዋርድ መልኩ ካልሆነ በቀር ከማያደርጋቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ- አንዴ ያሰረውን ተቺውን ፤ ያውም ብዙ ደጋፊ ያለውን መፍታት ነው፡፡ ኢህአዴግ እንደልጅ እልህ ይጋባል ማለቴ ነው፡፡ (ይህንን ስል የእስራችንን ኢፍትሀዊነት የተመለከቱትን ጩኸቶች መጥላቴ አይደለም፤ ያለ እነርሱ መንፈሳችን አይጠገንም ነበር፡በአደባባይ የምናመሰግንበት ቀን ይመጣል)
2ኛ. መጀመሪያ የተጠራጠሩበት እና ኋላ የዋጧት ጥርጣሬያቸው፤ ማለትም (ምርጫውን ተከትሎ) አመፅ ማስነሳት በሚሉት ጉዳይ ላይ እቅድ እንደሌለን ቢያምኑም እንኳን ምናልባት እምነታቸው ከተሳሳተ Risk መውሰድ አይፈልጉም፡፡ ( መጀመሪያም የቀለም አብዩት ዶክመንተሪ አዝማሚያ ያስታውሷል)
3ኛ. ምንም እንኳን ዓመፅም፤ሽብርም  የማስነሳት ፍላጎትም አቅምም፤  እንደሌለን ቢያምኑም የገዥው ፓርቲ ጠንካራ ተቺዎች መሆናችንን ስለሚያውቁ እና ስላልወደዱልን ፍርድ ቤት በምንመላለስበት ረዘም ያለ ጊዜ ባለው እስር ወቅት ቢያንስ የእስርን ምሬት እንድንቀምሳት ይፈልጋሉ፡፡ ቅጣትን ጨርሶ በነፃ መለቀቅ እንደማለት፡፡
4ኛ. ኢህአዴግ መፍረድ አይፈራም፡፡

ትላንትና መኢአድ ያወጣው የትግል ጥሪ መግለጫ ወያኔን ብቻ ሳይሆን አሜሪካንንም አደናበሯል።


 8 בAugust 2014 0 Comments
“መኢአድ ጠንካራ ድርጅት ነው።” በድንገት መኢአድ ቢሮ የደረሱ የአሜሪካ ዲፕሎማቶች
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ከኢሕአፓ ሕዋስ (ሴል) በመቀጠል በብቸኝነት ድርጅታዊ መዋቅሩን በማጥበቅ ታላቅ ስራዎችን የሰራው እና እየሰራ ያለው እንዲሁም በ97 ምርጫ የቅንጅት ማሸነፍ ታላቅ አስታውጾ የነበረው የፕሮፌሰር አስራት የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በትላንትና እለት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ባስተላለፈው የትግል ጥሪ የተደናገጡት ወያኔዎች ብቻ ሳይሆኑ የአሜሪካ መንግስት ዲፕሎማቶችም እንደሆኑ ከኤምባሲው የተገኙ መረጃዎች ጠቁመዋል።
ethiopolበትላንትናው እለት የመኢአድ እና የአንድነት አመራሮች በጋር በሰጡት መግለጫ መኢአድ ድርጅታዊ መዋቅሩን ተጠቅሞ የጎዳና ላይ አመጽ እንደሚጠራ እና ሕዝቡ በተጠንቀቅ እንዲጠባበቅ ለምርጫ ቦርድ እና ለወያኔም ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ይታወቃል። ይህ ያሰጋው ወያኔ እንደለመደው ሲራወጥ ሁኔታው እና የመኢአድ ጥንካሬ ያሰጋቸው የአሜሪካ ዲፕሎማቶች በዛሬው እለት የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ የሆነችዋ የኤምባሲው ዲፕሎማት በመኢአድ ጽ/ቤት በመገኘት አመራሮቹን ማነጋገሯ ታውቋል።
ከጠዋቱ በአምስት ሰአት በአስቸኳይ የፖለቲካ ጉዳይ በመግለጫው ዙሪያ ማብራሪያ ለመጠየቅ መኢአድ ቢሮ የመጡት እና በአሜሪካ ኤምባሲ የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ ሴት የተመሩት ዲፕሎማቶች የመኢአድን ጠንካራ ፓርቲነት መስክረዋል። በወቅቱ በውይይቱ ላይ እንዲገኙ የተጋበዙት አንድነቶች ኢንጂነር ግዛቸው ብቻቸውን በመምጣት ያልተጠየቁትን ሲቀባጥሩ መስተዋላቸውን ከዲፕሎማቶቹ ጋር በቦታው የነበሩ የኤምባሲው ምንጮች ገልጸዋል።
የመኢአድ አመራር በውይይቱ ወቅት በሃገሪቱ ያሉትን ችግሮች እንዲሁም ምርጫ ቦርድ መኢአድን ለማፍረስ እየሰራ ያለውን ደባ እና መንግስታዊውን በፓርቲዎች ላይ የሚደረገውን ሽብር በዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል። አንዳንድ ለመኢአድ እና ለአንድነት የሚቀርቡ ምንጮች ወያኒ አንድነት ውስጥ ባሉ ሰርጎገቦቹ ን ተጠቅሞ ከውህደቱ በኋላ የመኢአድን ድርጅታዊ መዋቅር ለማፈራረስ ደባ እንደወጠነ ሲጠቁሙ ውህደቱን እንደማይፈልገው ተደርጎ የሚወራው ለይምሰል መሆኑን አክለው ይገልጻሉ። ወያኔ የመኢአድ ድርጅታዊ መዋቅር ክፈረሰለት እፎይ እንደሚል ውስጥ አዋቂ ምንጮች ይናገራሉ።#ምንሊክሳልሳዊ

የኢህአዴግ ዲሞክራሲና የቴሌ ኔትዎርክ ተመሳሰሉብኝ


እኔ የምለው … አንዳንድ የመንግስት ተቋማት በእነሱ ብሶ ለምንድነው ቁጣ ቁጣ የሚላቸው? (“የማይመቱት ልጅ ሲቆጡት ያለቅሳል” አሉ!) ከምሬ እኮ ነው… እኛ የተበደልነው አርፈን ተቀምጠን እነሱ እየተመላለሱ ይቆጡናል፡፡ (ኧረ “ፌር” አይደለም!) ያውም እኮ ሳንደርስባቸው ነው፤ ቤታችን ድረስ እየመጡ – በኢቴቪ መስኮት፡፡ ከሁሉም አንጀት የሚያበግነው ደግሞ ትላንት እኛው በድምፃችን ይመሩናል ብለን የመረጥናቸው ተወካዮቻችን፣ ማታ ማታ በቲቪ እየመጡ መቆጣታቸው ነው፡፡ (ለ90 ሚ. ህዝብ ማስጠንቀቂያ አይፃፍማ!) ይሄን ሁሉ ያስቀባጠረኝ የሰሞኑ የኢትዮ- ቴሌኮም ቁጣ የተቀላቀለበት መግለጫ ነው፡፡ (እኛ ሳንቆጣ እሱ ይቆጣን?!)
በእርግጥ መጀመሪያ የምስራቹን ነበር ያስቀደመው፡፡ ግዙፍ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶቹን በስኬት ማጠናቀቁን በድል አድራጊነት ስሜት አበሰረን፡፡ (የቴሌ ድል የእኛም ድል ነው!) እንደመሰለኝ… የቁጣው መንስኤ የኢቴቪ ጋዜጠኛ ጥያቄ ነው፡፡ “ደንበኞች አሁንም የአገልግሎት ጥራት ችግሮች አሉ እያሉ ነው” የሚል ጥያቄ ሳያነሳ አልቀረም – ጋዜጠኛው፡፡ (ግን እኮ አልዋሸም!) ይሄኔ ነው ቁጣ ቁጣ ያለው – “አገልጋያችን” ኢትዮ-ቴሌኮም፡፡
አያችሁ… እዚህ አገር ሁሉ ነገር የተገላቢጦሽ ነው፡፡ በሌላው ዓለም ቢሆን እኮ የሚቆጣው ደንበኛ እንጂ አገልግሎት ሰጪው አይደለም፡፡ የሚቆጣው ህዝብ እንጂ መንግስት አይደለም፡፡ (መንግስትማ አገልጋይ ነው!) እኔ የምላችሁ… “ደንበኛ ንጉስ ነው” የሚለው አባባል እኛ አገር “ደንበኛ እርኩስ ነው” በሚል ተቀይሯል እንዴ? …በእርግጥ የኛ አገር ነጋዴዎች ወይም አገልግሎት ሰጪዎች “The Customer is always right” (ደንበኛ ሁሌም ትክክል ነው)  የምትለዋን አባባል ሲሰሙ “መስሎሃል!” እንደሚሉ ነገረ ስራቸው ያስታውቃል፡፡ እናም …ቢቆጡን፣ ቢያንገላቱን፣ መብራት ቢከለክሉን፣ ኔትዎርክ ቢነጥቁን፣ ውሃ ቢወስዱብን፣ ታክሲ የለም ቢሉን፣ ዘይት ቢያጠፉብን፣ ስኳር ቢያስወድዱብን፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ቢፈጥሩብን ወዘተ… ዝም ብለን መቀበል ብቻ ነው፡፡ ለምን “ደንበኛ ንጉስ”  ሳይሆን “እርኩስ ነው”
እናላችሁ… የኢትዮ ቴሌኮሙ ኃላፊ በኢቴቪ መስኮት ገጭ ብለው የመንግስት “የገቢ ኩራት” ስለሆነው መ/ቤታቸው ሽንጣቸውን ገትረው ተከራከሩ፡፡ የኔትዎርክ ማሻሻያው “ነዳጅ እንደሚበላ አሮጌ መኪና ሆነ” (አባባሉ የእኔ ነው!) ሲባሉ… አልካዱም፡፡ “በአንዳንድ አካባቢዎች አሁንም ኔትዎርክ ይጠፋል” የሚለውን ቅሬታም ተቀብለዋል፡፡ በመጨረሻ ግን “እናስ ምን ይጠበስ?!” ዓይነት ምላሽ ነው የሰጡት፡፡ “ይሄን ያህል ግዙፍ ፕሮጀክት ሲሰራ እኮ እንዲህ ዓይነት ችግሮች ያጋጥማሉ” አሉን፡፡ (ኔትዎርክ በዓመት አንዴ ጠፋ ብለን የምንሞላቀቅ “ቅንጡዎች”  አደረጉን እኮ!) በመካያውም… “የኔትዎርክም ሆነ ሌሎች ችግሮች በሂደት ይፈታሉ” … ብለው ገላገሉን፡፡ ይሄኔ ነው ኢህአዴግ ነፍሴ ትዝ ያለኝ፡፡ ኢህአዴግ ሁሌም ዲሞክራሲው ተንገራገጨ ወይም መልካም አስተዳደሩ ተሰናከለ አሊያም የሰብዓዊ መብት አያያዙ እያሳጣን ነው…በተባለ ቁጥር “በሂደት ይፈታል” ይለናል፡፡ የእሱ አይደለም የገረመኝ፡፡ የቴሌኮም መድገም ነው፡፡ (አወያይ መመሳሰል አሉ!)
ለዚህም ነው የኢህአዴግ ዲሞክራሲና የቴሌ ኔትዎርክ የተመሳሰለብኝ፡፡ (ሁለቱም የኋሊት ነው የሚጓዙት ልበል!) ለማንኛውም በሂደት ይፈታል ተብላችኋል – ኔትዎርኩ!!
addis admas

ደጋፊዎችን የማሰባሰብ ጥረት


Augest10/2014
የንቅናቄዓችን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ በህሊናና የፓለቲካ እስረኞች ሁሉ ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ መክበድ፤ በፀረ-ሽብርተኝነት ስም በሕዝብ ላይ የሚነዛው ወያኔያዊ ሽብር መብዛት፤ እስሩ፣ እንግልቱ፣ መሳደዱ፣ የሀብት ዘረፋው በየዕለቱ እየጨመረ መምጣት እና ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ ኑሮ እየከበደ መምጣቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከወያኔ ጋር ወሳኝ የሆነ ትግል መግጠሚያ ወቅት ላይ መደረሱ አመላካች ሆኗል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ የትግል መንፈስ መነሳሳት በተጨባጭ ከሚያረጋግጡ አመላካቾች አንዱ የግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አባል ለመሆኑ የሚፈልጉ ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን መጨመር ነው። ይህንን ለውጥ ተከትሎም ግንቦት 7 የአባላት ቅበላን ሥራ ለማፋጠን የሚረዱ እርምጃዎች ወስዷል። ሆኖም ግን በአባላት ቅበላ ወቅት ሊታለፉ የማይችሉ ጥንቃቄዎች መኖር እንዳለባቸው ደጋፊዎችም እጩ አባላትም ይረዳሉ ተብሎ ይታመናል።
በዚህም ምክንያት አሁንም እየጨመረ የመጣን ንቅናቄውን የመቀላቀል ፍላጎትን ለማስተናገድ፤ ለተግባራዊ ሥራዎች የተነሳሱ፣ ዓላማችንና ንቅናቄዓችንን የሚደግፉ ሆኖም ግን በተለያዩ ምክንያቶች በድርጅት አባልነት መቀላቀል የማይችሉ ወይም የማይፈልጉ አባላትን ለማሳተፍ የሚረዳ መዋቅር ማዘጋጀት ተገቢ መሆኑ ታምኖበታል። ስለሆነም እነዚህን ወገኖቻችን የትግላችን አካል ብቻ ሳይሆን የንቅናቄዓችንም አካል ለማድረግ እንዲቻል በአባላት ጉዳይ ሥር የደጋፊዎች ማስተባበሪያ መዋቅር እንዲደራጅ ተደርጓል። ይህ አደራጀት ግንቦት 7ን ለማዘመን እና ለኢትዮጵያዊያን ሁሉ የተመቸ ድርጅት ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አካል ነው። ይህ አደረጃጀት በአንድ በኩል የድርጅቱን ምስጢራዊት ለመጠበቅ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ ባሉ ፍላጎቶች መካከል ያለውን ቅራኔ ለመቅረፍ የቀረበ መፍትሔ ነው።
በዚህም መሠረት በአባልነት ለመመዝገብ ስለእናንተ ምስክርነት መስጠት የሚችል የግንቦት 7 አባል ማቅረብ ለጊዜው ያልቻላችሁ፤ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያት የግንቦት 7 ደጋፊ እንጂ አባል መሆን የማትፈልጉ ወገኖቻችን ግንቦት 7 ፍላጎታችሁን የሚያሟላ መዋቅር ማዘጋጀቱን በይፋ ያበስራል።
የግንቦት 7 ደጋፊ በግንቦት 7 የውስጥ ጉዳዮች የመወሰን፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት አይኑረው እንጂ የንቅናቄው ሙሉ ተሳታፊና ባለቤት በመሆኑ በልበ ሙሉነት “እኔም ግንቦት 7 ነኝ” ማለት ይችላል። የግንቦት 7 ደጋፊ እንደማንኛውም አባል ድርጅታዊ ሥራዎች ሊሰጡት ይችላል።
በደጋፊነት ለመመዝገብ ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ኢሜል፣ እድሜ፣ ጾታ፣ ከተማና የሚኖርበት ሀገር ብቻ የሚጠይቅ የድህረ ገጽ ቅጽ መሙላት ያስፈልጋል። ይህ ቅጽ በንቅናቄው ድህረ ገጽ ላይ ይገኛል። ደጋፊዎች እውነተኛ ስማቸውን የመስጠት ግዴታ የለባቸውም። አንድ ደጋፊ በየወሩ የሚፈቅደውንና የሚችለውን ያህል ገንዘብ እንደሚያዋጣ ይጠበቅበታል፤ ይህ የደጋፊነቱ አንዱ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል። ደጋፊ በሚኖርበት ከተማ በሚደረጉ የትግል እንቅስቃሴዎች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ ይጠበቅበታል፤ ይህም ሌላው የደጋፊነት መገለጫ ነው። ደጋፊዎች የንቅናቄው ሳምንታዊ ጋዜጣና ወርሃዊ ልዩ መልዕክት በግል ኢሜላቸው እንዲደርሳቸው ይደረጋል። ደጋፊዎች በተግባር በሚያሳዩት ተሳትፎ ከአባላት ጋር ቅርርብ በመፍጠር ወደ ከደጋፊነት ወደ አባልነት የሚሸጋገሩትን መንገድ ያመቻችላቸዋል።
በተለያዩ ምክንያቶች ራሳችሁን በህወሓትና ጀሌዎቹ መዋቅር ውስጥ ያገኛችሁና በወያኔ እኩይ ተግባራት የህሊና እረፍት ያጣችሁ የሕዝብ ወገኖች ይህንን መዋቅር ከግንቦት 7 ጋር በምስጢር ለመገናኛነት ተጠቀሙበት። በመከላከያና በፓሊስ እንዲሁም በራሱ በኢሕአዴግ ውስጥ ያላችሁ ወገኖቻችን ይህንን መስመር በግኑኝነት መመስረቻነት ተጠቀሙበት። በወያኔ የስለላ ወዋቅር ውስጥ ያላችሁም እድሉን ተጠቀሙበት።
በድህረ ገጻችን ላይ http://www.ginbot7.org/supporter-form/ በቀጥታ በመመዝገብ የግንቦት 7 ደጋፊ መሆን ይቻላል። ድረገጹ በማይከፈትባቸው ቦታዎች በ supporter@ginbot7.org ይፃፉ።

ETHIOPIA AND ITS PRESS – THE NOOSE TIGHTENS (THE ECONOMIST)

Ethiopia and its press – The noose tightens (The Economist)



A businesman reads a newspaper 14 May 20Bloggers and journalists who criticise the government are under the cosh
Aug 9th 2014 | ADDIS ABABA | Timekeeper
A RANKING that countries do not aspire to ascend is the one compiled by the Committee to Protect Journalists, a New York-based group. It reckons that Ethiopia is Africa’s second-worst jailer of journalists, ahead only of its ultra-repressive neighbour and bitter enemy, Eritrea. Cementing its lamentable reputation, on August 4th Ethiopia briefly resumed the trial of ten journalists and bloggers, nine of whom it has kept in prison since April; one is being tried in absentia. The court proceedings are to start again in earnest on August 20th.
The ten are accused of several offences, including breaches of the country’s controversial anti-terrorism laws. These include having links to banned opposition groups and trying to cause instability via social media. The government says the journalists and bloggers are connected to two groups that it deems terrorist organisations: the Oromo Liberation Front, a rebel outfit that seeks a better deal for Ethiopia’s largest ethnic group, which predominates in the south; and Ginbot 7, a leading opposition movement formed after widespread protests following Ethiopia’s general election in 2005.
The arrests are part of a broader clampdown on the opposition and the media. In June Andargachew Tsigie, Ginbot 7’s exiled secretary-general, was detained in transit through Yemen and flown to Ethiopia. He had previously been sentenced to death in absentia in two separate trials.
On August 4th Ethiopia’s ministry of justice upped the ante by filing fresh charges against five magazines, a newspaper and their publishers, alleging that they were “engaging in incitements that could undermine national security” and promote discord. Readers view the five popular magazines, which have criticised government policies, as an alternative to the rosy narratives of state media. With a general election due next year, this seems to be making the ruling party twitchy.
From the print edition: Middle East and Africa

የአንዳርጋቸዉ ትዉስታዎች


“በእኛ እምነት ታሪክ ከነባራዊ ሁኔታ ዉጭ በምኞትና በዘፈቀደ አይሰራም። የሚሰራ ቢሆን ኖሮ ነገስታቱና አምባገነኖቹ ዘሬም በዙፋናቸዉ ላይ በተገኙ ነበር። ባለንበት ወቅት የኢትዮጵያ ህዝቦች መስቀለኛ መንገድ ላይ ቆመዉ ከዚህ ወዴት እንደሚሄዱ ግልጽ ኢየባልሆነበት ሰዐት ሥልጣን ላይ ያለዉም ሆነ የሌለዉም የግሉን የተስፋ ጎዳናን እዉነተኛዉ የወደፊት ጎዳና አድርጎ የሚያይ ከሆነ ዛሬም እንደ ትናንቱ ከታሪክ መማር አልቻልንም ማለት ነዉ”።
“ከዲሞክራሲ ጋር ሲወዳደር ፍትህ ለሚለዉ ጽንሰ ሀሳብ “ኢትዮጵያዊኛ” ቃላቶች ያሉን መሆኑ የሚያስረግጠዉ ነገር ቢኖር ፍትህ ከማንነታችን ጋር የተቆራኘ መሆኑን ነዉ። ኢትዮጵያዉያን ፍትህ ሲጓደል “በህግ አምላክ” ብለዉ በዳያቸዉን ለማስቆም የሚያሰሙት ጩኸት ፍትህ ከፈጣሪያቸዉ የተሰጠ ከሰብዓዊነታቸዉ ተነጥሎ የማይታይ እሴት አድርገዉ እንደሚመለከቱት የሚያመለክት ነዉ። በምድር ላይም ፍትህ የሚሰጥ ዳኛ ጠፍቷል ብለዉ ሲያስቡ እጃቸዉን ወደ ፈጣሪያቸዉ ዘርግተዉ አንተዉ ፍርዱን ስጠና የሚሉት ከፈጣሪያቸዉ ፍጹምነት የሚመነጭ እዉነተኛ ዳኝነት አለ ብለዉ ስለሚያምኑ ነዉ። ከዚህ በላይ ባጭሩ የተባለዉ የሚጠቁመዉ በኢትዮጵያዉያን ባህልና ስነ ልቦና ዉስጥ የፍትህ ጽንሰ ሀሳብ ያለዉን ትልቅ ትርጉምና ቦታ ነዉ”።
የታሪክን ነባራዊነት፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ለፍትህ የሚሰጠዉን ከፍተኛ ቦታና ለነጻነት ያለዉን አመለካከት በተመለከተ ከዚህ በላይ ያሰማናችሁን ሁለት አዉዶች በሁለት የተለያዩ መጽሐፎቹ ዉስጥ የጻፈዉ ዛሬ ፍትህ አልባ በሆነዉ የወያኔ ስርዐት ዉስጥ ለፍትህ፤ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ ሲል ለፍተኛ ዋጋ እየከፈለ ያለዉ አንዳርጋቸዉ ጽጌ ነዉ። አዎ የፍትህና የነጻነት አርበኛዉ አንዳርጋቸዉ በግልጽ አንዳስቀመጠዉ ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍትህ እስከነ ስሙ ሙልጭ ብሎ በመጥፋቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ሁለት እጆቹን ወደ ሰማይ ዘርግቶ እባክህ አምላኬ “ወይ ዉረድ ወይ ፍረድ” እያለ ፈጠሪዉን እየተማጸነ ነዉ። በእርግጥም ፍትህ ፈጣሪያችን ያደለን ትልቅ ማህበራዊ እሴት ነዉ፤ ሆኖም ይህንን የፈጣሪ ስጦታ እኛን የመሰሉ ሌሎች ሰዎች መጥዉ ሲቀሙንና እንዳሰኛቸዉ ሰረግጡን አንረገጥም ብለን እራሳችንን ነጻ ማዉጣትና የተቀማነዉን ፍትህ ከወያኔ ዘረኞች ቀምተን መልሰን ማህበራዊ እሴት የማድረጉ ኃላፊነት የእኛ የራሳችን ነዉ እንጂ የፈጣሪ አይደለም። ፈጣሪያችን ፍትህና ነጻነትን አንዴ ሰጥቶናል እነዚህን የፈጣሪ ስጦታዎች እንዳንቀማ መጠበቅና ከተቀማን ደግሞ ታግለን ማስመለስ ያለብን እኛ ብቻ ነን።
አንዳርጋቸዉ ጽጌ የአማራዉ ህዝብ ከየት ወዴት በሚለዉ መጽሐፉ ታሪክ ከነባራዊ ሁኔታ ዉጭ በምኞት ወይም በዘፈቀደ እንደማይመራና ከትናንት ታሪካችን ካልተማርን የምንደግመዉ ትናንትናና ከትናንት ወዲያ የሰራናቸዉን ስህተቶቻችንን አንደሆነ በግልጽ አስገንዝቦናል። ይህ የአንዳርጋቸዉ ማስገንዘቢያ ያነጣጠረዉ ለመብቱና ለነጻነቱ መከበር ለሚታገለዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ህዝብ ረግጠዉ እየገዙ ዝንተ አለም መኖር ለሚፈልጉ የወያኔ ዘረኞችም ጭምር ነዉ። ለመሆኑ አንዳርጋቸዉ ከታሪክ አልተማርንም ማለት ነዉ ሲል ምን ማለቱ ነዉ? . . . “አልተማርንም” የሚለዉ ቃል ለአንድ ሰዉ የሚነገር ቃል ሳይሆን ለብዙኋን የሚነገር ቃል ነዉ። በዚህ ብዙኋን ዉስጥ በአንድ በኩል በየዘመኑ እየረገጡ ከሚገዙት የገዢ መደቦች ጋር የሚታገለዉ የኢትዮጵያ ህዝብ አለ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ህዝብን ረግጠዉ እየገዙ መኖር የሚፈልጉ የገዢ መደቦች አሉ። የኢትዮጵያ ህዝብ በ1966 ዓም የፊዉዳል ገዢ መደቦችን አንኮታኩቶ ከጣለ በኋላ ለሚቀጥሉት 17 አመታት ሰዉ በላዉን የደርግ ስርዐት ተሸክሞ ኖሯል። በ1983 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ አሁንም ወታደራዊዉን የደርግ ሰርዐት በህዝባዊ አመጽ ማስወገድ ችሎ ነበር፤ ሆኖም አሁንም ይህ ህዝብ የታገለለት ድል ባለቤት መሆን ባለመቻሉ ዘረኛ አምባገነኖች መዳፍ ዉስጥ ገብቶ ቁም ስቅሉን እያየ ነዉ። አንዳርጋቸዉ ጽጌ ይህንን የጥፋት ዑደት በሚገባ ተገንዝቦ ነዉ ከታሪክ አልተማርንም ብሎ የነገረን።
በ1966 ዓም ጩኸታችን በሙሉ የፊዉዳሉ ስርዐት እንዲፈርስ ነበር እንጂ የምናፈርሰዉ ስርዐት በምን ይተካል ለሚለዉ ጥያቄ መልስ ስላልነበረን በወቅቱ በስራዉ ጠባይ የተነሳ ተደራጅቶ የነበረዉ የወታደሩ ክፍል ስልጣን ተረክቦ አገራችን 17 አመት ሙሉ የደም ባህር ዉስጥ እንድትዋኝ አድርጓታል። የደርግን ስርዐት ለማፍረስ በተደረገዉ ትግል ዉስጥም ከ1966ቱ ስህተታችን ምንም ባለመማራችን መሳሪያ ከታጠቀ ኃይል ሁሉ ጋር ጉሮ ወሸባዬ መዝፈን ጀመርን። ደርግን የሚዋጉ ኃይሎች ሁሉ የህዝብና የአገር ወዳጆች እየመሰሉን በየጫካዉ እየሄድን ተቀላቅለናቸዉና ዛሬ ይሄዉና እኛዉ እራሳችን ያጠናከርናቸዉ ኃይሎች ስልጣን ይዘዉ ካፈረሱት ስርዐት በከፋ መልኩ አገርንም ህዝብንም እያፈረሱ ነዉ። ደርግ ከፊዳሉ ስርዐት ዉድቀት ምንም ባለመማሩ ሃያ አመት ሳይሞላዉ እሱም እንደ ፊዉዳሉ ስርዐት የታሪክ ቆሻሻ ዉስጥ ተጥሏል። ከፊዉዳሉም ከደርግም ስርዐት ዉድቀት መማር ያልፈለጉት የዛሬዎቹ ዘረኞች ደግሞ የማይቀረዉን ዉድቀታቸዉን እየጠበቁ ነዉ። የወያኔ ዘረኞች ከታሪክ አለመማር ካሁን በኋላ ሊገርመን ወይም ሊያጠያይቀን አይገባም፤ እነሱ ወደዱም ጠሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ያስተምራቸዋል። ዛሬ ዋናዉ ቁም ነገር ወይም ትልቁ ጥያቄ እኛ ካለፉት ሁለት ግዙፍ ስህተቶቻችን ተምረናል ወይ የሚለዉ ጥያቄ ነዉ፡፡ ስራችን የወያኔን ስርዐት ማፍረስ ብቻ ነዉ ወይስ ከወያኔ መፍረስ በኋላስ ለሚለዉ ጥያቄ መልስ አለን። ወያኔን እያፈረስን ስንሄድ ከማፍረስ ጎን ለጎን ወያኔን የሚተካ ስርዐት እየገነባን ነዉ ወይስ ሩጫችን ሁሉ ማፍረሱ ላይ ብቻ ነዉ ያተኮረዉ።
የወያኔን ስርዐት ለማፍረስ በሚደረገዉ ትግል ዉስጥ የተቃዋሚ ኃይሎች መሰባሰብና በአንድነት መቆም ቁልፍ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፤ ሆኖም በእኛ እምነት እጅግ በጣም ከባዱና ዉስብስቡ ስራ ወያኔ የፈጠረዉን ዘረኛ ስርዐትና ቆሻሻ ባህል ማፈራረስና በምትኩ ሌላ መገንባት ነዉ እንጂ ወያኔን ማስወገዱ አይደለም። ወያኔ በህዝብ የተጠላና የተተፋ ስርዐት ስለሆነ በራሱ ዉስጥ በሚፈጠር ቀዉስ ወይም በአንድ እራሱን ለህዝባዊ አመጽ ባዘጋጀ ጠንካራ ድርጅት ተጠራርጎ ሊጠፋ የሚችል ድርጅት ነዉ። ለአገራችን ለኢትዮጵያ በጎ የምንመኝና ዛሬ ወያኔን በተለያየ መልኩ የምንፋለም የነጻነት ኃይሎች አጅግ በጣም ሊያሳስበን የሚገባና አገራችን ኢትዮጵያም በቀላሉ የማትወጣዉ ማጥ ዉስጥ የምትገባዉ ወያኔ ከእነዚህ ሁለት መንገዶች በአንዱ ከወደቀ ነዉ። ይህንን ታሪካዊ ጥፋት እዉን ከመሆኑ በፊት መቀየር የምንችለዉ ደግሞ ወያኔ ከወደቀ በኋላ ሳይሆን ዛሬ ለመዉደቅ ሲንገዳገድ ነዉ።
አንዳርጋቸዉ አገራችን ብዙ አደጋዎች ፊቷ ላይ አንደተደቀኑባት በትክክል ካሳየን በኋላ አደጋዎቹን አንዴት መከላከል አንዳለብንም በቃላትና በንድፈ ሃሳብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በተግባርም በረሃ ዉስጥ ገብቶ መሬት ላይ እየተኛ ያሳየን የተግባር ሰዉ ነዉ። ዛሬ የወያኔ ዘረኞች አንዳርጋቸዉን አስረዉ የሚያሰቃዩት የአንዳርጋቸዉ ዕቅድና የጀመራቸዉ ስራዎች የእነሱን ቆሻሻ ስርዐት ጠራርጎ ኢትዮጵያን እንደሚያጸዳ ከወዲሁ ስለተረዱ ብቻ ነዉ። በእርግጥም አንዳርጋቸዉ የሽብርተኞች ድርጅት መሪ ቢሆን ኖሮ ጨዋዉና አርቆ አስተዋዩ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያሸብረዉ ሰዉ ሲታሰር ደስታዉን ነዉ እንጂ ቁጣዉንና ሀዘኑን አይገልጽም ነበር። የአንዳርጋቸዉ መታሰርና አንደ ማዕበል ገንፍሎ የወጣዉ ህዝባዊ ቁጣ ወለል አድርጎ ያሳየን ነገር ቢኖር አትዮጵያ ዉስጥ አሸባሪዉ ማን እንደሆነ ነዉ።
ወያኔን የሚተካ ጤነኛ አካል ሳናዘጋጅ በጅምላ ወያኔ ይወገድ አንጂ ከዚያ በኋላ ያለዉ አይቸግርም የሚለዉ አባባል አደገኛ አባባል ነዉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ መስማማት አቅቶን ለእነዚህ የቀን ጅቦች የምንሰጣቸዉ ግዜና በየግላችን በተናጠል የምናደርገዉ ጉዞ አገራችን ኢትዮጵያን ከድጡ ወደ ማጡ ይዟት የሚሄድ አጅግ በጣም አደገኛ ጉዞ ነዉ። “እኔም አንዳርጋቸዉ ነኝ” ስንል እናት አገራችን ኢትዮጵያን ከእንደነዚህ አይነት አደጋዎች ለማዳን ምንም አይነት መስዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተናል ማለት ነዉ።
የለበስነዉ ልብስ ከመጠን በላይ ሲቆሽሽ ያለን ምርጫ የተዘጋጀ ቅያሪ ካለን እሱን ቀይረን የቆሸሸዉን ማጠብ ነዉ፤ ቅያሪ ካሌለን ግን አዲስ ልብስ መግዛት ነዉ ያለብን እንጂ መቼም ካላበድን በቀር በቆሻሻ የጀቦደ ልብስ ለብሰን አደባባይ አንወጣም። ከ1966ቱና ከ1983ቱ ታሪካዊ ስህተቶች የተማርን ኢትዮጵያዉያንም ማሰብና ማድረግ ያለብን እንደዚሁ ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ ስርዐት ከመጠን በላይ ቆሽሿልና በበረኪና ታጥቦ የሚጸዳ ከሆነ በፍጥነት መታጠብ አለበት፤ አለዚያም ወያኔን ከማስወገዱ ሂደት ጋር ጎን ለጎን የሚሄድ አዲስ ስርዐት በጋራ መገንባት እንዳለብን ለአፍታም ቢሆን ልንዘነጋዉ የማይገባን ኢትዮጵያዊ አደራ ነዉ።
ዛሬ እጁ በዘረኞች ተይዞ የሚሰቃየዉ አንዳርጋቸዉ ጽጌ የኑሮ ጓደኛዉን፤ አንድ ፍሬ ልጆቹንና ወንድሞቹን ትቶ ከሞቀዉ የአዉሮፓ ኑሮ በረሃ ወርዶ የማደራጀትና የማስተባበር ስራ መስራት የጀመረዉ እነዚህ ከላይ የጠቀስናቸዉን የአገራቸን ዉስብስብ ችግሮች በሚገባ ስለተገነዘበና ያለፉት ስህተቶቻቸን ላለመድገም የቆረጠ ሰዉ ስለሆነ ነዉ። አንዳርጋቸዉ ከታሪክ እንማር ሲል የፍትህና የዲሞክራሲ ትግላችን አላማና ግብ ወያኔን መጣል ብቻ ሳይሆን ካሁን በኋላ በሰላምና በእኩልነት ሊያኖረን የሚችል ስርዐትም መገንባት አለብን ማለቱ ነዉ። አንዳርጋቸዉ ፍትህ የምንለዉ ጽንሰ ሃሳብ ከኢትዮጵያዊ ማንነታችን ጋር የተቆራኘ ነዉ ሲል ይህንን ከማንነታችን ጋር የተቆራኘ ትልቅና እጅግ በጣም አስፈላጊ ማህበራዊ እሴት በዘረኞች ተቀምተን እንኳን ሃያ ሦስት አመት አንድ ምሽትስ ቢሆን እንዴት ተኝተን እናድራለን ማለቱ ነዉ። አንዳርጋቸዉ ለአገራችን አንድነትና ለዲሞክራሲ መብታችን መከበር እስከ ሞት ድረስ መሄድ አለብን ሲል ዲሞክራሲ ያልሞረደዉ አንድነት ወይም አንድነት ያልሞረደዉ ዲሞክራሲ እስካልገነባን ድረስ ትግላችን አያቆምም ማለቱ ነዉ።
ዛሬ በአለም ዙሪያ በአራቱም ማዕዘን ኢትዮጵያዉያን “እኔም አንዳርጋቸዉ ነኝ” በሚለዉ መፈክር ዙሪያ የተሰባሰቡት የአንዳርጋችዉ አላማና የአርባ አመት ጉዞ የእነሱም አላማና የወደፊት ጉዞ ነዉ ብለዉ ስለሚያምኑ ነዉ። “እኔም አንዳርጋቸዉ ነኝ” ማለት እኔም ልክ እንደ አንዳርጋቸዉ ጽጌ፤ እንደ እስክንድር ነጋ፤ ሠላማዊት ሞላ፤ በቀለ ገርባ፤ አንዱአለም አራጌና ዞን ናይን ብሎገርስ የመብት፤ የነጻነት፤ እኩልነትና የአገር አንድነት ጉዳይ ያንገበግበኛልና ለእነዚህ እሴቶች መከበር እኔም አንደነዚህ ጀግኖች ኢትዮጰያዉያን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነኝ ማለት ነዉ።በአለማዉ የሚጸና፤ ለአላማዉ ግብ መምታት የተዘጋጀና በህይወቱ የቆረጠን ሰዉ ደግሞ ከድል ወዲህ ማዶ የሚያቆመዉ ምንም ምድራዊ ኃይል የለም።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!