Monday, December 23, 2013

የሕወሓት አደገኛ የዘረኝነት መርዝ እና የናዚ ፍልስፍና


መጀመርያው ዓለም ጦርነት ማገባደጃ ቦኋላ በጀርመን ማደግ ጀምሮ የነበርው ´´የናሺናል ሶሻሊስት ፓርቲ´´ የናዚ የፖለቲካ ዘይቤን በማስፋፋት ፣ የፋሺስቶች የቀኝ ክንፍ እንቅስቃሴ በዛን ወቅት በዋናነት ይታገል ፣ ይዋጋ ነበረው አንዱ ኮሚኒስቶችን ነበር ፡፡ እነዚህን ክፍሎች ዒላማ ካደረገበት ምክንያት አንዱ ፣ በወቅቱ በዓለማችን ዙርያ እየተጠናከረ የነበረውን ፣ የኮሚኒስቶች እንቅስቃሴ ለመቋቋምና ፣ በስራቸው እየተደራጀ የነበረውን የሰራተኛውን ክፍል (working class ) ከኮሚኒስቶች ነጥሎ በናዚስቶች ስር ለማሰለፍና ነበር ፡፡

የናዚ ፍልስፍና መሰረት ፣ የ አርያን ታላቅ ዘር (Aryan master race ) ከሌሎች የሰው ፍጠረት ዘሮች ሁሉ የላቀና ፣ የተመረጠ ሕዝብ እንደሆነ ያምናሉ ፡፡ እነሱ የሚሰጡትን ገጸ-ባህሪያት የማያሟላ ፣ እንደ ሰው ካለመቁጠራችወም በላይ ``በስህተት ወይም ሳይፈለጉ ተፈጥረው ``የተገኙ ነገሮች ተደርገው ስለሚታዩ ፣ መደምሰስ ወይም መጥፋት አለባቸው ብለው ያምኑ ነበር ፡፡ በዚህም የተነሳ ታሪክ እንደመዘገበው ከነሱ ዝርያ ውጪ ናቸው ብለው ፣ በተለያየ ዘርፍ የመደብዋቸውን ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሌሎች ዜጎችን በየማጎርያ ካንፑና (concentration camp)፣ በየእስር ቤቱ እየተሰበሰቡ በሚያሰቅቅ ሁኔታ በጋዝ ጢስ ፣ በጥይት እሩምታና በተለያየ መንገድ እንደጨረሱዋቸውና ፣ ከፊሎቹንም ፣ በጣም አሰቃቂና ፣ኢ-ሰባዊ በሆነ መንገድ ፣ ሰውነታቸውን ለህክምና ምርምር ይጠቀሙባቸው ነበር ፡፡ ከዚያም አልፈው ሄደው፣ የሰውን ልጅ ክቡር ፍጡር ከእንሳት በታች አድርገው በመቁጠር ፣ ቆዳቸውን ለማስታዎሻ (souvenir) ለመብራት አንፖል ማጌጫና ፣ ለቤት ማሳመርያ ቁሳቁስ ይጠቀምባቸው እንደነበር ፣ ዛሬ ከነማስረጃው በተለያዩ የማጎርያ ካንፕ ፣ ሙዝየም ውስጥ ተቀምጠው ማየት ይቻላል ፡፡

እነዚህ ከአርያን ዘር ውጪ ያሉትን ፣ መፈጠር አይገባቸውም ነበር ብለው የመደቧቸውን ፣ ይሁዲዎችን ፣ ጂብሲዎችን ፣ የአዕምሮ ህመምተኞችን ፣ አካለ ስንኩላንን፣ ጥቁሮችን ፣ ከነሱ ሃይማኖት ውጪ ያሉትን ፣ እንደ የጆሃቫ እምነት ተከታዮችን ፣ የፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸውንና ፣ የተለየ ጾታዊ አቀራረብ እምነት የነበራቸውን ፣ ከሰባዊ ማንኛውም ፍጡር በታች አድርገው ከማየታቸውም በላይ እንደ የግል መገልገያ ቁሳቁስ አድርገው ፣ አዕምሮዋችን መገመት ከሚችለው በላይ ፣ ኢሰባዊ ድርጊት ይፈጽሙባቸው ነበር ፡፡ የፓርቲ መመሪያቸውም ከላይ የተዘረዘሩትን ከነሱ ውጭ የተፈጠሩትን ፣ የማጥፋት መብት እንዳላቸው ተደርጎ እንዲታመንበት ተቃኝቶ የተዘጋጀ ንድፈ -ሃሳብ ወይም የፖለቲካ ዘይቤ( ideology) ስለነበር ፣ አብዛኛው ሕዝባቸውን በዚህ ፍልስፍና አሳምነው ፣ አሳስተው ከጎናቸው ማሰለፍ ችለው ነበር ፡፡

አርያን የሚለውን ፣ ቃሉን መጠቀም የጀመሩት ሰዎች ፣ ለዚህ የዘረኝነት ተግባር መጠርያ ለማድረግ ሳይሆን ፣ ለአንድ አካባቢ ሕዝብ (ፖርቶ ፣ ኢንዶ አውሮፓውያን ...ወዘተ) መጠርያ ወይም መለያ ለማድረግ ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም ናዚዎች ይህንን እውነታ ቀይረው ፣ ትክክለኛ ሕዝብ ማለት በነሱ በነሱ እምነት ፣ ነጭ ፣ ሰማያዊ የዓይን ቀለም ያለውና ፣ ወርቃዊ ቀለም ጸጉር ያለውና ፣ (white, blue eyes and blond hair) የነሱን የፖለቲካ መስመር የሚከተል ...ወዘተ ብለው ያምናሉ፡፡

ይህ አደገኛ በታሪካችን የሚታወቅ በዓለም ሕዝብ ላይ ያደረስው እልቂት ፣ ያስከተለው አካላዊና ስነ-ልቦናዊ ጉዳት በግልጽ ከመታወቁም በላይ ፣ ዛሬም የነሱ ርዝራዦች ፣ በተለያየ ቅርጽ ፣ እንደ አዲሱ የፋሺስት ንቅናቄ (neonazi´s ) እና ፣ በአውሮፓ በህጋዊ የፖሊቲካ ሽፋን ስር ተደራጅተው በግልጽ ይንቀሳቀሳሉ ፡፡ ቅርጻቸውንና ፣ ዘዴያቸውን በመቀያየርና ፣ ያለውን ዲሞክራሲያዊ ህጋዊ መንገድ እንደ ሽፋን በመጠቀም፣ እጅግ ወደ ቀኝ ያጋደለ የዘረኛነትን ዓላማ ፣ የሚያራምዱ ፣ ይፋዊና ፣ ህቡዕ የፖለቲካ ድርጅቶች በማቋቋም እስካሁን ድረስ፣ በምዕራቡ ዓለም በይፋ ሲንቀሳቀሱ እናያለን ፡፡ አንዳንዴ በዓለም ዓቀፍ የኤኮኖሚ ቀውስ ምክንያት ፣ የሃገራቸው ኤኮኖሚ ሲዳከምና ፣ ችግራቸው ሲጠና ፣ ተራውን ሕዝባቸውን ፣ ለዚህ ችግር ምክንያት አድርገው የሚያቀርቡት ፣ የውጪ ዜጎችን ወደ ሃገራቸው ባብዛት መግባትና ፣ የነሱን ሕዝብ ስራና ጥቅም ስለሚካፈሉ እንደሆነ አድርገው ምክንያት እየሰጡ ፣ በተለይ በቀውሱ የተጠቁትን ያሳምኗቸዋል ፡፡

ሕዝብ እነሱን ቢመርጥ ፣ የውጪ ዜጎችን አባረው ፣ ለነሱ የሚጠፋው ንዋይ ለሃገራቸው እንደሚያውሉና ከችግር እንደሚያወጧቸው ቃል ይገቡላቸውል ፡፡ በዚህ የምርጫ አጀንዳ በለስ ቀንቷቸው ስልጣን ሲይዙ ፣ አዳዲስ ጸረ የውጪ ዜጎች ህጎች በማውጣት ከነሱ የተለየ ዘር ፣ ቀለምና ፣ የሃይማኖት እምነት ያላቸውን ፣ የሃገሪቷ ዜጎች ባልሆኑት ላይ ፣ ከፍተኛ ጫና በመፍጠር ፣ ሃገራቸውን ጥለውላቸው እንዲወጡ ከፍተኛ ግፊት ያሳድራሉ ፡፡ ይህ በተለይ እንደ
ብዙዎቻችን ሃገራችንን ጥለን በተሰደድነው ዜጎች ላይ የሚያደርሱብን መንፈሳዊ ጫናና መሸማቀቅ ቀላል እንዳልሆነ እናቀዋለን ፡፡
የናዚዎች የፖለቲካ አካሄድ ከነሞሶሎኒ ፋሺስቶቹ ጋር ብዙ የሚጋሩት እምነት ስለነበራቸው፣ በሃገራችንም ለአጭር ጊዜም ቢሆን ፣ በፋሺስት ወራሪ ጠላት በግድ ተጭኖብን ከነበረው የዘረኝነት ህግና ፣ በወቅቱ በነበሩት ወገኖቻችን ላይም ሆነ በሌሎች ሃገሮች ላይ ይደርስ የነበረው መከራ ስንሰማ ፣ ዘረኝነት ምን ያህል አስከፊ ገጽታ እንደነበረው ከወላጆቻችንና በአህጉራችን ላይ በዚህ ጨካኝ የዘረኝነት ስርዓት ውስጥ ካለፉት ሃገሮች ታሪክ ብዙ ተምረናል ፡፡

በሃገራችንም ፣ በአንዳንድ ኋላ ቀር ባህላችንንና ፣ ካለማወቅ ፣ ከብዙዎቻችን የተለየ የአኗኗር እምነት፣ ልዩ ሙያዊ ተሰጥኦ የነበራቸውን ፣ ወገኖቻችንን ፣ ቡዳ ፣ ፋቂ ፣ ቀጥቃጭ፣ መጫኛ ነካሽ ፣ .....ወዘተ እየተባለ አንዱ ከሌላው የተሻለ ወይም ያነሰ ሆኖ የሚታይበት ፣ የዘር ፣ የሙያና ፣ የእምነት አድሎዋዊ አካሄድ ስለነበር ፣ ከነዚህ ወገኖቻችን ጋር ፣ በጋብቻና በማህበራዊ ኑሮ የማንቀላቀልበት ፣ አሳፋሪ ባህል ነበረን ፡፡ ሆኖም ይህንን አስቀያሚ ባህል ፣ ባለፉት ዓመታት በሂደት ፣ በዓለማዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ትምህርት ፣ በሕገ-ደንባችን ...ወዘተ ፣ ለማስወገድ እየተጣረ ነበር ፡፡

ሆኖም ካለፉት 21 ዓመታት ወዲህ ወያኔ ስልጣን ላይ ከወጣ ቦኋላ ፣ ጎጠኝነት ሕጋዊ ሽፋን ተሰጥቶት አንቀጽ ወጥቶለት ፣ በአዋጅ አጊጦ ፣ ሕዝባችንን ዘረኛ በሆነ ፣ ጎጥንና ቋንቋን መሰረት ባደረገ ``ፌደራላዊ አስተዳደር`´ በሕዝባችን ላይ በሃይል ጭኖ ለየት ባለ መልክ ተኳኩሎ ቀረበልን ፡፡ የህንን የማይቀበሉ ወገኖቻችንን ሲያሳድድ ሲያጠፋና ፣ በግልጽ ኢፍትሃዊ -የዘረኛነት አካሄድ ሲከተል እድሜያችንን አጋምሰናል ፡፡ ይህ ዘረኛ ስርዓት ከተዘረጋ ቦኋላ ፣ ለረዥም ዘመናት አብሮ በኖረ ሕዝባችን ማሃል ፣ በዘመናችን አይተን የማናውቀው ፣ የጎጥና ፣ የሃይማኖት ጥላቻ ውስጥ ለውስጥ በአገዛዙ ፣ እንደ ፖሊሲ እየተነደፉ ልዩነትን በማስፋፋት ፣ እርስ በእርስ ከፋፍለው ፣ አዳክመውን የነሱን ሥርዓት ለማራዘም ሲሞክሩ ማየት የተለመደ ሆንዋል ፡፡

ይህ በአገዛዙ ፣ ዘዴውንና ፣ ቅርጹን እየቀያየረ ፣ ተራ በተራ በሕዝባችንና ፣ በዕምነታችን መሃል ጣልቃ እየገባ እርስ በእርስ በማናቆር ያደርስ የነበረው ችግር በመጠኑ ተሳክቶለት ቢሆንም ፣ በእቅዳቸው መሰረት እንደፈለጉት ገና አልተሳካም ፡፡ ይህ ተንኮል የገባቸው ክፍሎች እንዲያውም በተቃራኒው ፣ አልፎ አልፎም ቢሆን ፣ የተለያዩ የኃይማኖት አባቶችና ፣ በፖለቲካውም መስመር ፣ አብረው ተቃውሞዋቸውን ማሰማት ጀምረዋል ፡፡

ይህ ፍልሚያ ቀጣይነት ባለው መንገድና ፣ በተሻለ በተቀናጀ ዘዴ እየተደራጀ ፣ እየተሰባሰበ ፣ ትግሉን አስተባብሮ ወደ አንድ አቅጣጫ ለማምጣት እየተካሄደ ያለው አዝማሚያ ግን ገና አስተማማኝ ባይሆንም፣ ጅምሩ ተስፋ የሚሰጥ ነው፡፡
ምክንያቱም ፣ አብዛኛው የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ፣ ውስጥ ለውስጥ እያደገና ፣እየተስፋፋ የመጣውን የዘረኝነት አደጋ አሳሳቢ ደርጃ ላይ መድረሱን አልተቀበሉም ፡፡ በዚህም ምክንያት አገዛዙ በቀላሉ ይወገዳል ብለው ስለሚያምኑ ፣ አብዛኛው ጉልበታቸውን የሚያጠፉት ፣ የሌለ የምርጫ ውድድር መድረክ እንደተፈጠረ ፣ እኔ እበልጥ ፣ እኔ እበልጥ አይነት ፉክክር በማድረግ ነው ፡፡ የአንድነቱ ክፍል ነኝ ከሚለው ፣ በተሻለ የጎጥ ፖለቲከኞቹ እየተቀናጁና ፣ እየተደራጁ፣ እየተቻቻሉ ፣ አጀንዳቸውን በማገባደድ ላይ ናቸው ፡፡ ባጠቃላይ ለአንድነት ቆምኩኝ የሚለው ክፍል ፣ ይህንን አደጋ አጢኖ ስላላየው ፣ በወሬ ፣ ስለ ሕብረት ፣ ጥምረት ፣ ውሕደት ፣ አስፈላጊነት ከመቆዘም ውጪ ፣ ተቻችለው የእውነት ተባብረው ለመቆም ገና አልወሰኑም ፡፡

አንዳንድ የምናያቸውም ሙከራዎችም ፣ በራሳቸው የፖለቲካ አጀንዳ ዙርያ የሚቀራረቡ ፣ ለስልጣን ክፍፍልና ፣ ሚዛን ለመድፊያ የተማከለ ሆኖ ፣ በአዕምሮዋቸው ለፈጠሩት ``የምርጫ ውድድር`` የተነደፈ እንጂ ፣ በእውነት ይህንን ስርዓት ለማስወገድ ተፈልጎ ፣ለጊዜው ልዩነትን ፣ ለእውነተኛ የምርጫ ጊዜ አቆይቶ ፣ መጀመርያ ሃገራችንን ከአንባገነናዊ ሥርዓት ነጻ ለማውጣት ተብሎ ፣ ተቻችሎ አብሮ ለመቆም የታለመ አይደለም ፡፡ እንዲያውም አሁን ፣ የኅብረት አሰባሳቢዎቹ ብዛት የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችን ቁጥር አልፎ ሊሄድ ስለሆነ ፣ ለነሱም ሌላ ``የኅብረት አሰባሳቢ `` ቡድን ማቋቋም አስፈላጊ እንደሆነ መገመት አይከብድም ፡፡
የአገዛዙ ዓላማው ፣ የጎጥ ፖለቲካን በሕዝባችን መሃል ማስፋፋትና ፣ ይህም ቦኋላ ሊያስከትል የሚችለውን የመገነጣጠል አደጋ ያሰጋናል እስካልን ድረስ ፣ በማንኛውም መንገድ ይህንን ከፋፋይ ሥርዓት ተባብሮ ለማስወገድ አለመጣር፣ ወይም እነሱ በሚሄዱበት መንገድ እየተጓዝን የችግሩ ተባባሪ መሆን ፣ መሀከል ምንም ልዩነት የለውም፡፡ የዚህን አደጋ ክብደት መቀበል ካልፈለግን ፣ ምርጫችን የሕዝባችንን ስቃይ ማርዘም ፣ አገዛዙ እንዲቆይ መርዳትና በመጨረሻም ፣ ለሃገራችን መበታተን ምክንያት መሆኑን መቀበል አለብን ፡፡

የዚህ ጽሁፍ ዋናው ዓላማ ፣ ከላይ በአጭሩ ጠቅሼ ለማሳየት የሞከርኩት ፣ በሃያኛው ክፍለዘመናችን በጀርመን ተከስቶ የነበረው አስቀያሚ የናዚ /የፋሺስቶች የዘር አድልዎ ፖሊሲ ምልክቶቹን ፣ በሃገራችን ፣ በአንዳንድ በተቃዋሚው አካባቢ ባሉም ምሁራንም ጭምር ፣ በአንዳንድ ድህረ-ገጾችና የፓልቶክ የመወያያ ክፍሎች ሲሰሙና ፣ ሲንጸባረቁ ያየሁትን አደገኛ አዝማሚያ፣ ስጋቴን ለወገኖቼ ለማካፈል እንጂ ፣ ባለሙያው ሆኜ አንባቢያንን ለማስተማር አይደለም፡፡
የናዚዝም ፣ ወይም እራሳቸውን የአርያን ማስተር ሬስ (Aryan master race ) ብለው የሚጠሩት ዘርኞች ዋና መለያ አካሄዳቸው ፣ የሌላውን ሰው ሕልውና መካድ ፣ በሕዝብ መሃል ያለውን ታሪካዊ ትስስርን አለመቀበል ፣ ከአንድነቱ ይልቅ በልዩነቱ ላይ ማተኮር ፣ በሕዝቦች መሃል አጥር ማጠር ፣ የግንኙነቱን ድልድይ ማፍረስ ፣ በሰዎች ልጆች መሃከል ሰፊ የማበላለጥና ፣ ሚዛኑ የተንሻፈፈና ቅጥ ያጣ የወገንተኛነት አካሄድ ማስፋፋት ነው ፡፡

ይህ አይነት ግልጽ የዘረኛነት አካሄድ ፣ ትላንት የወያኔው መሪ ፣ `` ከወርቅ ዘር በመወለዴ እኮራለሁ `` ያሉን ፣ ሕዝብን ከሕዝብ የማበላለጥ ዘረኛ ዓላማ ስንቃወም ሰንብተን ፣ ዛሬ ደግሞ ፣ አውቀው ሆነ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ ሳያጤኑት ፣ እንደዚህ አይነት ከፋፋይ ፣ የፋሺስት ዘረኛ ፖለቲካዊ ቋዋንቋ ማሰማት የጀመሩትን ፣ ቁጭ ብሎ ማዳመጥ እየተለመደ መምጣት ጀምሮዋል ፡፡
ዛሬ ከአንዳንድ ተቃውሞን እናስተባብራለን ከሚሉ ፣ ሊያስወግዱ ከሚፈልጉት ስርዓት ባልተለየ መንገድ እየተጓዙ ፣ ቆመንለታል የሚሉት ሕዝብ ያልጠየቃቸውን ፣ እሱ ከሌላው የምበልጥ ነኝ ያላለውን ፣ እሱ ያልፈለገውን በስሙ እንወክለዋለን እያሉ ፣ በሕዝባችን መሃል ፣ ጥላቻንና ፣ መራራቅን የሚጋብዝ ፣ አላስፈላጊ ማበላለጥ ፣ ባልተለመደ መልኩ ሲካሄድ ስንሰማ ፣ ከማሳዘኑም በላይ እያሰጋን ሄድዋል ፡፡
በአንድ የታሪክ ሂደት አስገዳጅነት በተከሰተ ሁኔታም ይሁን ፣ ተፈጥሮ በቸረው ልዩነት ፣ እንደ ጌጣችን ልናየው ፣ የሚገባን ታሪካችንን ፣ አንዱ ከሌላው ፣ የተመረጠ ፣ የተሻለ ፣ ቆንጆ ፣ ጸጉረ ዞማ ፣ አፍንጫ ሰልካካ ፣ ጎበዝ ተዋጊ ፣ ታላቅ ሕዝብ ፣ ወርቅ ሕዝብ .......ወዘተ የመሳሰሉ ፣ በጣም ኋላ ቀር የሆኑ ዘረኛ ፣ ቅጽላዊ ማበላለጦችን በሕዝባችን መሃል ፣ በአለንበት በሃያ አንደኛው ዘመን ማዳመጡ ጆሮ ያሳምማል ፤ አንገት ያስደፋል ፣ ተስፋ ያጨልማል ፡፡ ይህ አይነት አላስፈላጊ ወገንተኝነት ፣ ቆመንለታል ለሚሉት ክፍል ከሌላው ወገኑ እንዲነጠልና ፣ የጥቃት ኢላማ እንዲሆን ከመርዳት ባሻገር የሚጠቅመው ነገር የለም ፡፡
በእርግጥ በማንኛውም ወገናችን ላይ በተናጠል የሚደርሰው ፣ በጎም ይሁን ጉዳት የጋራችን መሆኑን መቀበል አለብን፡፡ የማንኛውም ክፍል ወጋናችን በተናጠልና በተራ በሚደርስበት ፣ መሰቃየት ፣ መታሰር፣ መፈናቀል ፣ መጋዝ ፣ መዋረድ ፣ ለሌላውም ህመም ሆኖ ሲሰማው ኖርዋል ፡፡ ለመፍትሄውም አብሮ ተዋድቋል ፣ ታግሏል ፣ አብሮ በደም የተሳሰረ አንድነት ገንብቷል ፡፡ ያም እየተደናቀፈም ቢሆን ወደፊ ይቀጥላል ፡፡

በተለምዶ ፣ በአባቴ የትውልድ ሃረጌ የዚህኛው ዘር ነኝ ፣ በእናቴ የዚያኛው የእከሌ ወገን ነኝ እንደምንለው ሁሉ ፣ ሁላችንም በኢትዮጵያዊነታችን ከአማራውም ፣ ከኦሮሞውም ፣ ከሃዲያውም ከሁሉም የሐገራችን ሕዝብ ጋር ትስስር ስላለን ፣ የትኛውም ወገናችን ፣ በተናጠልም ይሁን በጋራ ለሚደርስባቸው ጥቃት፣ የራሳችን ጥቃት መሆኑ ተሰምቶን፣ ከማንኛውም የተገፋ ወገናችን ጎን ቆመን ጥቃቱን በጋራ ልንከላከል ይገባል ፡፡ ኢትዮጵያ የሚለው ሁላችንንም የሚያገናኝ ማእከል ነው ካልን ? እኔ በኢትዮጵያዊነቴ ዶርዜነት አለብኝ፣ በኢትዮጵያዊነቴ አፋርነት አለብኝ ፣ በኢትዮጵያዊነቴ አማራነት ፣ በኢትዮጵያዊነቴ ኦሮሞነት ....ወዘተ አለብኝ ብለን አምነን ፣ በተግባር በክፉም ሆነ በደጉ ጊዜ አብረን ተደጋግፈን ስንቆም ነው ፣ እውነተኛ ኢትዮጵያዊነታችንን በተግባር የምናስመሰክረው፡፡

አንዳንዴ ሰዎች እራሳቸው ባልመረጡት መንገድ እንዲሄዱ ፣ ስለሚገፉ ፣ ሰዎች በተናጠል ለሚደርስባቸው ጥቃት እራሳቸውን ለመከላከል በሚያደርጉት ጥረት ፣ የሌላውን ህልውናና ፣ መብት እስካልተጋፉና ፣ ላጠቃላዩ ሕብረት ችግር እስካልሆኑ ድረስ ፣ በሚያመቻቸው መንገድ የመታገል መብታቸውን መቀበል ብቻ ሳይሆን ማገዝና ፣ ከጎናቸው ሆኖ ብቻቸውን አለመሆናቸውን ማሳየት ወገናዊ ግዴታ ነው ፡፡
ይህ አይነት ወገናዊ ትብብር ፣ ለየብቻ መፍትሄ ፍለጋን ለማበረታት ሳይሆን ፣ የላላውን ለማጥበቅ ፣ የራቀውን ልብ ለማቅረብ ፣ የተጎዳውን መንፈስ ለመጠገን ፣ ይበልጥ የሚያስተሳስረን ፣ በሂደት የገነባነውን በጎ ትሪካችንን የሚንከባከብና ፣ የማይጠቅመንን አስወግደን ለሃገራችን አንድነትና ፣ ለሕዝቦቿ እኩልነት ለሚደረገው ትግል ጽኑ የአንድነት መሰረት እንደሚገነባ በማመን ነው ፡፡
ለሰባዊ መብቶች (human rights)መቅደም ስንታገል ፣ ዘር ፣ ሃይማኖት ፣ ቀለም ፣ ጾታ ፣ ታላቅነት ፣ ጀግነት ፣ የመሳሰሉትን ``እንደ መለኪያ `` አስቀምጠን ሳይሆን ፣ ወይም በቡድንና ፣ በግለሰብ የተደራጁና ያልተደራጁ በሚል ስሌት ከፋፍለን ሳይሆን ፣ በዚህ ምድር ላይ ለተፈጠረ ፣ ለሰው ልጅ የተሰጠው ተፈጥሮዋዊ መብቱ የተጣሰ በመሆኑ ብቻ ነው ፡፡
በሌላው ወገናችን ላይ የሚደርሰው፣ እስር፣ እንግልት ፣ መፈናቀል ፣ የሚሰማን ፣ የእኛ በምንለው ላይ ብቻ ሲደርስ ከሆነ ? የሌላው ወገናችን ስቃይና መከራ ፣ እንደራሳችን የማይሰማን ከሆነ ? ሕዝባችንን ያስተሳሰረውን ሰንሰለት እየበጣጠስን ፣ ለጎጣችን ፣ ለመንደራችን ፣ ብቻ የምንጨነቅ ከሆነ፣ በእውነት እንደ ናዚዎቹ ፣ በዘረኞች በሽታ እንደተለከፍን መቀበል አለብን ፡፡

ትላንት ያልተመችን ፣ ሌሎች ብቻቸውን የሄዱበት ጸረ አንድነት የጥፋት መንገድ ነበር ብለን አሁንም የምናምን ከሆነ ? ፣ ይህንን አካሄድ እኛ ስንደግመው ልክ የሚሆንበት መንገድ ስለሌለ ፣ የምንከተለው የትግል አቅጣጫ ፣ ለጋራ ችግራችን ወደ የጋራ መፍትሄ የሚያደርሰ መንገድ የሚያመቻችልን እቅድ ስንነድፍ ነው ፡፡ በጋራ ታግለን ፣ የምናመጣው ሰላም ፣ ዕድገትና ፣ ፍትህ የሰፈነበት ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የብዙውን ፣ አለ የምንላቸውን ችግሮቻችንን መፍቻ ቁልፍ ስለሆነ ፣ በየትኛውም አቅጣጫ የምናደርገው ግፊት ፣ ወደ እዚህ አቅጣጫ አቅርቦ የሚያሰባስበን መሆን ይኖርበታል፡፡

የሕዝባችን ጥያቄም ባይሆን ፣ ለረዥም ጊዜ ፊደል በቆጠረው ጎጠኛ (elite) እንወክለዋለን ብለው ወደ ሕዝባችን በሚገፉት አጀንዳ የተጎዳው አንድነታችንን ለመጠገን ፣ በተመሳሳይ መንገድ በእልህ መሄድ ፣ እነሱን መተባበር እንጂ ለሃገር እንደማይጠቅም መታወቅ አለበት ፡፡ በእልህ የሚወሰድ አቅዋም ፣ ለማንኛችንም የሚበጅ አይሆንም ፣ ይበታትነናል፣ በዚህ ደግሞ ማንም አይጠቀምም ፡፡ በሳይንስ እንደተረጋገጠው ፣ ስሜታዊነት ሚዛኑ በዝቶ ካጋደለ ፣ ዕውቀት ወይም ጥበብን የያዘው የአዕምሮ ክፍላችን ስራውን ይቀንሳ፡፡(when emotions is high intelligence is low) የዚህም ውጤት የሚያስከትለውን አደጋ ለማስረዳት አንባቢዎቼን መናቅ ይሆንብኛል ፡፡

ወደድንም ጠላንም የመገንጠልን ዓላማ በሚገፉ ጎጠኛ ኢሊቶችና ፣ በሥርዓቱ ተባባሪነት ይገፋ የነበርው የዘረኞች ዓላማ ፣ ወደ ሕዝባችን እየገባ ፣ ከምንገምተው በላይ እየተራባ ፣ በብሔራዊ አንደንታችን ላይ አደጋ እንዳንዣበበ ያስተዋሉት ጥቂቶች ናቸው ፡፡ የአንድነቱ ደጋፊዎች ነን ከምንል ፣ የጎጥ ፖለቲካ አራማጆች በተሻለ እይተደራጁ ፣ እየተሰባሰቡ እንደሆን መካድ የዋህነት ነው ፡፡
ሕዝብ ደግሞ ፣ መሪ እስከሌለውና ፣ አደራጅቶ ትክክለኛውን አቅጣጫ የሚመራው እስከሌለው ድረስ፣ ቁጥሩ ስለበዛ ምንም ሊሰራ አይችልም ፡፡ በተግባር የምናየውም የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ሕዝባችን ብቻውን እንደተውት ነው፡፡ በዚህ ላይ ከአንድ አቅጣጫ ብቻ በቀጣይነት በሚፈስለት ጥንፈኛ አመለካከት አይሳሳትም ማለት አይቻልም ፡፡ በተለያዩ የታሪክ አጋጣሚ ፣ ሕዝብ የተሳሳተ አቅዋም ሊወስድ እንደሚችል በተደጋጋሚ ታይቷል ፡፡

በእነዚህ ጎጠኛ አስተሳሰብ ባላቸው የሚገፋውን የዘረኝነት ጥፋት ፣ እንወክለዋለን የሚሉት ሕዝብ አቅዋም እንደሆነ አድርገን ተስፋ ቆርጠን ፣ በወገኖቻችን ላይ ዕምነት ማጣት የለብንም ፡፡ እንደዛ ማመን የጀመርን ከሆነ ፣ ለጎጠኞች እጅ እየሰጠን እንደሆነና ፣ እኛም የችግሩ ተባባሪ መሆን እንደጀመርን ማመን አለብን ፡፡ በሕዝባችን የሚቀርበው መሰረታዊ ጥያቄና ፣ የተማረው (ኢሊት) በሚፈጥረው ችግር መሃከል ያለውን ልዩነት ማስመር ካልቻልንና ፣ ሁለቱን ካምታታን ፣ ወደ ተሳሳተ ድምዳሜ እንዳይወስደን መጠንቀቅ አለብን ፡፡ እየመጣ ያለውን ችግር አቃለንም ሆነ አጋነን ሳናየው ፣ እንደ ሁኔታው ቅደም ተከተል ተደራጅተን ልንታገለው ይገባል፡፡
ያለው አገዛዝ ፣ የጎጠኞችን ፍላጎት በእጥፍ አጩሆ የሚያደነቁረን እንጂ ፣ የአብዛኛውን ፣ አንድነቱን የሚፈልገው ሕዝባችን ድምጽ ስለታፈነ ፣ ባለመስማታችን ልንጠራጠር አይገባም ፡፡ የሕዝባችንን እውነተኛ ፍላጎት በተለያየ አጋጣሚ ቀዳዳ ሲያገኝ አሳይቶናልና ፣ አሁንም ምንም የተለወጠለት ዓዲስ ነገር ስለሌለ ትግሉ ይቀጥላል ፡፡ እስሩ ፣ እመቃው ፣ ችግሩ ፣ ስደቱ ፣ እንደቀጠለ ሆኖ ፣ አሁንም አብዛኛውን ክፍል ያገለለ አንባገነናዊ ሥርዓት በሰፈነበት ሁኔታ፣ ከመታገል ሰንፈን ፣ እንዲሆንልን የምንመኘውን ፣ ከላይ እንዲፈቀድልን በተስፋ ደጅ እየጠናን ተጃጅለል ማጃጃሉ አይጠቅመንም ፡፡
ካለፈው እንኳን የቅርብ ታሪካችን ፣ ይህ ሥርዓት ሁሌ ግፊት በሚደርስበት ወቅት ፣ ``ለመደራደር `` በሚል ስንት አዛውንቶች ፣ ስልጣን እንቁልልጭ እያላቸው ፣ ሰነድ እያስፈረመ ፣ ከሕዝብ አጋጭቶ ሁኔታውን ፣ በግልባጩ ለራሱ እንደተጠቀመበት መርሳት፣ ትልቅ የፖለቲካ የዋህነት ነው ፡፡ መደራደር የሚባል እንኳን ነገር ቢኖር ፣ ትግልን ሳያቀዘቅዙ ፣ ትጥቅን ሳያላሉ ፣ በስልት ግፊት በማሳደር እንጂ ፣ የገነባነውን የትግል ስሜት እራሳችን ከናድንለት ቦኋላ ፣
ተርግጦ መገዛት እንጂ ፣ አገዛዙስ ለምንድነው ለመደራደር የሚፈልገው? ለዛውም እኛው መላ እየመታንላቸውና ፣ እየተረጎምንላቸው እንጂ ፣ ከእነሱ የሰማነው ምንም ተስፋ የለም ፡፡
እንዲያውም አገዛዙ ከሃገራችን አልፎ እጁን አርዝሞ ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በየስርቻው ለአድር ባዮች እየዘራ፣ በጅት መድቦ፣ ያሰማራቸውን የውሸት ተቃዋሚዎች ፣ ``በየስብስቡና፣ በየሕብረቱ `` ውስጥ እየጠቀጠቀ አመራሩን በራሱ ሰርጎ ገቦች ሊያሲዝና ፣ መድረኩን ሊያጣብብ ሲሞክር እየታዘብን ነው ፡፡ ይህ ቀድመው መድረኩን ይዘው ሊሰራ ባማይችል መንገድ ጀምረው ካኮላሹት ቦኋላ ፣ ሰዉ ተስፋ ቆርጦ ሁለተኛ የእውነቱንም እንዳይሞክር ፣ ወይም በእውነቱ እና እነሱ በፈጠሩት መሃከል የተምታታ ሁኔታ ለመፍጠር የሚያደርጉት ጥረት ነው ፡፡

እነዚህ ሰረገው የሚያስገብዋቸው የሰለጠኑ አደናባሪዎች ፣ መንገድ ለይ እንደተንጠለጠለ የሕዝብ ቴሌፎን ፣ ገንዘብ እያቃሙዋቸው ፣ በቀሚስና ፣ በንዋይ እያባበሉዋቸው የሚያስለፈልፋቸው ፣ አስመሳይ ተቃዋሚዎች አንዱ እግራቸውን ጠላት ሰፈር ፣ ሌላውን ተቃዋሚው ሰፈር ተክለው ፣ እንደ ቱቦ አስተላልፉ የተባሉትን ውዥንብር (disinformation) በመረጃ ስም እየበተኑ ፣ አሁንም የተቃዋሚው ክፍል ተጠናክሮ እንዳይደራጅ የሚችሉትን ሁሉ እንደቀድሞው ለማደናገር ሲሞክሩ የምናየው ነው ፡፡ ተቃዋሚውም ፣ ማን ምን እንደነበር የራሱ (trackrecord) ስለሌለው ፣ ትላንት ከውስጣችን ወጥተው ፣ አስር ጊዜ እየካዱን ሲመለሱ ፣ የሚቀበላቸው በእቅፍ አበባ ነው ፡፡

ከአዲሱም ጠቅላይ ሚኒስቴራችን በትክክል በሚገባን ቋዋንቋ የሰማነው ነገር ቢኖር፣ ሊመልሱ የተዘጋጁት የሕዝባችንን ጥያቄ ሳይሆን ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴር የጀመሩትን ``ራዕይ`` በተጠናከረ መንገድ እውን ማድረግን ነው ፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ ወጥቶ ``የሃዘናቸው ተካፋይ መሆኑን`` ለዓለም ሕዝብና ፣ ለእኛ ሊያሳዩን ሲነሱ ፣ ከፍተኛ ድጋፍ አለን ፣ በጀመርነው መንገድ እንቀጥላለን ማለት መሆኑን የማይገባን ከሆነ ፣ አስተርጓሚ ሊያስፈልገን ነው ፡፡ ወይንም አንዳንዶች በሌላ ዘረኛ ስሌት ሊነግሩን እንደሚፈልጉት `` ችግራችን ሥርዓቱ ሳይሆን ፣ የመሪው ማንነትና ፣ የመጣበት ክፍልን ነበር የምንቃወም`` ብለው በግልጽ ይነግሩን እንደሆን እንጂ፣ ተስፋ ማየት ገና ምንም አልጀመርንምና ለገላጋይነት አንጣደፍ ፡፡

ባጠቃላይ ይህን ሁሉ ዘርፈ ብዙ የጋራ ችግራችንን፣ ለማስወገድና አደጋውን ለመከላከል የምንችለው፣ ባልሆነ ተስፋ እራሳችንን በማታለል ፣ ወይም በእልህ እነሱ በሄዱበት የጎጥ መንገድ በግልባጩ ተጉዘን ሳይሆን ፣ ሰከን ብለን ፣ ትግላችንን ሳናቀዘቅዝ ፣ ትጥቃችንን ሳናላላ ፣ ለዋናው ብሔራዊ ደህንነታችን ስንል መለስተኛ ልዩነቶቻችንን በይደር አቆይተን ``cease-fire`` ይህች ሓገር እንደ ሃገር እንድትቀጥል የምንፈልግ የአንድነት ሃይሎች ፣ ጋባዥ ሳይጠራን ፣ አስተናጋጅ ሳያስፈልገን፣ ግርግር ፣ ድግስ ፣ አሜሪካ ኦባማ እያልን ``መቀላወጥ`` ሳናበዛ ፣ እንደ ጥንቱ አባቶቻችን ፣ ተፈላልገን ፣ ተጠቃቅሰን ፣ ተሰባስበን ፣ ተደራጅተን፣ ብሔራዊ አጀንዳችንን ቀርጸን በጋራ አምርረን መታገል ስንጀምር ብቻ ነው፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ሁሌ በራሱ መንገድ ይጠብቃታል ፡፡ብስራት ኢብሳእኛም በቀና የአንድነት መንፈስ እንተባበረው ፡፡

ምኒልክ ሳልሳዊ

የአቦይ ስብሀት ነገር!

ከአሁን በፊት በዚሁ ርዕስ ፅሁፍ እንደፃፍኩ አስታውሳለሁ . አጋጣሚ ሆኖ ዛሬም ይህን ፅሁፍ ለመፃፍ በምነሳበት ወቅት ከዚሁ ርዕስ ሌላ ሀሳቤን በአንድነት ጭምቅ አድርጎ ሊገልፅልኝ የሚችል ርዕስ ሊመጣልኝ ስላልቻለ እንደገና በዚሁ ርዕስ መጠቀሙን ወደድኩ አባይ ስብሀት በልበወለድ ዓለም የተፈጠሩ ሰው *ቢሆኑ ኖሮ እጅግ በጣም አጨቃቃጪ , አነጋጋሪና የተለየ ስብዕና ያላቸው ገፀ ባህርይ ሆነው የተቀረፁ እጅግ በጣም የተዋጣለት ገፀ ባህርይ ይሆኑ ነበር . የሚገርመው ነገር በእውኑ ዓለም ያሉ ሰው ሆኖው ሳለ እንዲህ ዐይነት አነጋጋረና ግራ አጋቢ የሆነ ገፀ ባህርይ ያላችው ሰው መሆናቸው ነው .:: ለዚህ ሳይሆን አይቀርም ብዙውን ጊዜ በሚናገሩት ነገር ሁሉ ትኩረት ሳቢ ሆነው የምናገኛቸው . ለዛሬ ባለፈው በህዳር 17 ቀን 2006 ዓ.ም. በአዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ዲፓርትመንት ተጋብዘው በተናገሩት ላይ ይሆናል ትኩረት የማደርግው . አቦይ ስብሀት በዩኒርሰቲው ተገኝተው ፖለቲካዊ ሀሳባቸውን ለተማሪዎች እንደሚያካፍሉ ዜናውን እንደሰማሁ ደግሞ ምን ሊሉ ይሆን ብዬ ነበር ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር በመሆን እዚያ የተገኘሁት . እኔም የዩኒቨርሲቲው ተማሪ መሆኔ ጠቀመኝና የተማሪነት መታወቂያን አሳይቼ ወደ አዳራሹ ዘለኩ . አባይ ስብሀት ሙሉ ለሙሉ ጥቁር የሆነ ሱፍ ለብሰው , ከፊት ለፊት በተደረደሩ መደዳ ወንበሮች ላይ ተሰይመዋል . ከዚያ ድፎ ዳቦ እንዲቆርሱ ተደረገና ወደ ዝግጅቱ , ዋናው ጉዳይ ተገባ . በአንድ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ዲፓርትመንት ተማሪ ጥያቄ አቅራቢነት አቦይ ስብሀት ለጥያቄዎቹ ሰፋ ያለ መልስ መስጠት ጀመሩ . ለዛሬ ትኩረቴን እጅግ ከሳቡኝና ግርምት ከፈጠሩብኝ የአቦይ ስብሀት ንግግሮች የተወሰኑትን እዚህ ላይ እያነሳሁ ሀሳብ እሰጥባቸዋለሁ ::
1, . ሀገር ማለት
አቦይ ስብሀት " ሀገር ማለት ህገ መንግስቱ ነው ; . ሌላ ነገር አይደለም " . የሚል ነገር ተናግሯል ይሄ ለእኔ ምን ማለት እንደሆነ ግለፀው ብባል ; . እንዲህ በሌላ ምሳሌ ላስቀምጠው እችላለሁ ትዳር ምንድነው ለሚለው ጥያቄ " . ትዳር ማለት የጋብቻ ሰርቴፍኬት ማለት ነው 
ብሎ የመመለስ ያህል ነው . ይሄ አነጋገር ስሜት ሊሰጥ ይችላል ? ! ትዳርን ትዳር የሚያድርገው የጋብቻ ሰርቴፍኬት አይደለም ; የጋብቻ ሰርቴፍኬት ትዳሩን ህጋዊ ያደርገው እንደሆነ እንጂ ራሱ ትዳር ሊሆን የሚችል ነገር አይደለም ሀገርም እንደዚያ ነው ; . ያለ ህገ መንግስት ሀገር ሊኖር ይችላል ; ሀገር ከሌለ ግን ህግ መንግስት የሚባል ነገር አይኖርም ህገ መንግስት የተፈጠረው በጣም ትናንት በሚባል ጊዜ ሲሆን ; ሀገሮች የተፈረጡትና የኖሩት ግን ለብዙ ሺህ ዓመታት ነው ለምሳሌ ; . የእኛ ሀገር ታሪክ ብንወስድ እንኳ የሀገሪቷ ታሪክ ከሶስት ሺህ ዓመት በላይ ሲሆን በህገ መንግስት ስም መተዳዳር የጀመርንበት ጊዜ ሲታይ ደግሞ አንድ መቶ ዓመትም አልሞላንም . ለነገሩ በሀገራችን በጠመንጃ ጉልበት እንጂ በአግባቡ በህገ መንግስት የሚያስተዳድረን መንግስት እስከዛሬ አላገኘንም ወይም አልፈጠርንም .

2 . ስለኤርትራውያን 

አቦይ ስብሀት ስለኤርትራውያን ሲናገሩ " ኤርትራውያን ከኢትዮጵያውያን በላይ ነው ኢትዮጵያዊነትን በጣም ይፈልጋሉ ; በአንፃሩ ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉት የኤርትራ መሬት ነው ህዝቡ አይደለም . አሰብ ቀይ ምናምን ይላሉ . ​​" ብለው እርፍ ! ምንም እንኳ ንግግሩ እጅግ በጣም የሚገርም ቢሆንም የአርትራውያንን ኢትዮጵያዊነት ከአቦይ ስብሀት መስማቴ ጥሩ ለውጥ ነው እላለሁ ; ኤርትራውያን ከእኛ በላይ , ከኢትዮጵያውያን በላይ ኢትዮጵያዊነትን ይሰማቸዋል የሚለውን ግን ቀልድ ነው ሊሆን የሚችለው . ሲጀመር እንዲህ ብሎ ለመናገር በመጀመርያ ህዝቡ ስለዚህ ጉዳይ ያለው አቋም ተጠንቶ ; በደንብ በተጠናቀረ መረጃ ተደግፎ ነው መቅረብ የነበረበት ከሁሉም በላይ እጅግ አድርጎ የሚያሳዝነው ደግሞ ኢትዮጵያውያን የኤርትራን መሬት እንጂ ህዝቡ አይፈልጉትም መባሉ ነው . እኔ የማውቀው በተቃራኒው ነው ; የኢትዮጵያ ህዝብ ለኤርትራውያን ጥልቅ የሆነ ፍቅር እንዳለው ነው ; አሁን ይሄ ሁሉ ነገር ከተፈጠረ በኋላ እንኳ እንደ ራሱ ህዝብ እንደወንድም ህዝብ እንጂ እንደ ጎሮቤት ህዝብ ወይም እንደባዕድ ህዝብ የሚያያቸው አይደለም አቦይ ስብሀት የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ህዝቦች የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ነገሮች እየሰከኑ ሲሄዱ ለምሳሌ በኤርትራ ያለውን ስርዓት ሲቀየር በሆኑ ቅርፅ ተባብረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ግንኙነታውን ማጠናከር የሚችሉበት እንድል እንዳለ ; በፌዴሬሽንም በኮንፌደረሽንም በሌላም መልኩ የነበራቸውን አንድነት መመለስ የሚችሉበት ሁኔታ ይፈጠራል ብለው እንደሚያምኑ የተናገሩት በዚያን ቀን ከተናገሯቸው አዎንታዊ ንግግሮች አንዱ ነበር . ስለ ኤርትራው ፕሬዚደንት ሲናገሩ ኢሳይያስ የሚፈልገው አጀብና እዩኝ እዩኝ ማለት እንጂ ሌላ ነገር አይደለም ብሏል ; . እርሱ ገንዘብም አይፈልግም ብሏል የምን ገንዘብ እንደሆነ ግልፅ ባያደርጉትም የእርዳታ ገንዘብ ማለታቸው ሊሆን እንደሚችል መገመት የሚቻል ነው ሀበሻ አይደሉ ; . እኛ እና እርሱ ልዩነታን እዚህ ላይ ነው ማለታቸው መሆን አለበት በቅኔ ! ይልቅ የሰሞኑ አንዱ ገጠመኝ ልንገራችሁ አንድ ኤርትራዊ ከሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ ከኢትዮጵያውያን ጋር ተደባልቆ ኢትዮጵዊነት ተቀብለው ነው እንደዚህ ወጣት ያሉ ኤርትራውያን በነፃ ከእኛ ዜጎች ጋር ወደ ሀገራችን እያመጡ ያሉት ያስባል . ሻዕቢያ ካልላካቸው ምንም ችግር የለውም ; ኢትዮጵያም ሀገራቸው ነው ድሮም ቢሆን በሻዕቢያ ፕሮፖጋንዳ ተታልለው ነው እንገንጠል ብለው የሄዱት እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ ስለጠላቸው አልነበረም . አቦይ ስብሀት እንዳሉት እነዚህ ኤርትራውያን እየመጡ ያሉት ትክክለኛ ኢትየጵያውያን እነርሱ ናቸው ተብሎ ከሆነ ግን በማን መንግስት እየተዳደርን እንደሆነ መጠየቃችን አይወሬ ይሆናል . " እናንተ 
ከኤርትራውያን ያነሳችሁ ኢትዮጵያውያን ናችሁ " የሚለን መንግስት መቼውም ቢሆን ጤነኛ መንግስት ሊሆን አይችልም ; መንግስትም የመሆን እድል የለውም .

3, የቀበጡ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች

በእስር ላይ ስለሚገኙ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች ተጠይቀው ሲመልሱ " ይሄ ስርዓት በስንት መስዋዕትነት የመጣ ስርዓት ነው ; በዚህ ላይ ሁኔታ በመጣ ስርዓት ላይ ማንንም እንዲቀብጥ ሊፈቀድለት አይገባም . መለስ በፓርላማ ስላንዳንድ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች አስመልክቶ ሲናገር ጉዳት እስካላደረሱ ድረስ ወንጀለኛ መሆናቸውን እያወቅንም እንታገሳቸዋለን ሲል ሰምታችሁት ይሆናል ተሳስቷል ማንም ሰው በህገ መንግስቱ ላይ በስርዓቱ ላይ የመቅበጥ ምልክት ሲያሳይ ጊዜ ሊሰጠው አይገባም ; እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል :: ስለዚህ ማንም ቀበጥ በስርዓቱ ላይ እንዲጫወትበት አንፈቅድም " ብሏል . እንግዲህ በእርሳ c ው አባባል ከሄድን እነ አንዷለም አራጌ , እነ ርዕዮት ዓለሙ ; እነ ውብሸት ታዬ , እነ እስክንድር ነጋ በቅብጠት ነው የታሰሩት ማለት ነው በእስር ጉዳይ ላይ ቀብጠት አለ እንዴ . !ለዚያውም ብእኛ ሀገር ! የኖርዌይ መንግስት እንደዚያ ቢል ብዙም ላይገርም ይችላል ; ምክንያቱም የእስር ቤታቸው ሁኔታ እጅግ የሚያማልል ነው . ከእኛ አንፃር ስታየው ! በቃልቲ ለመታሰር እንዴት ነው ቅብጠት የሚሆነው . እነርሱ የታሰሩት የነፃነት የፍትህ ጥያቄ እንስተው እንጂ ቀብጠው አይመስለኝም . እኔም ይሄን ጉዳይ አንስቼ ቅብጠት ሊሆን እኮ ነው በአቦይ ስብሀት አተያይ ! ጠያቂው በመቀጠል " እነዚህ የታሰሩት ጋዜጦኞች በአንድ በእኩል ወንጀለኛ ተብለው ታስሯል በሌላ በእኩል የሀሳብን በነፃነት የመግለፅ ታጋዮች ተብለው በዓለም አቀፍ እየተሸለሙ ነው ይሄ ሁለቱ ነገር አይጋጭም ወይ ? " ብሎ ሲጠይቃቸው , ፈገግ ብለው ያሰራው አካል እኮ አይደለም እየሸለማቸው ያለው ! በማለት ተሳልቋል ::

4 . ስለሰማያዊ ፓርቲ

" ሰማያዊ ፓርቲ የምን ፓርቲ እንደሆነ ግራ የሚገባ ነው ; የሃይማኖት ፓርቲ ይሁን የፖለቲካ ፓርቲ ይሁን አይታወቅም " አሉ .በመቀጠል ደግሞ " ሰማያዊ ፓርቲ ሙስሊም ወንድሞቻችን ሲል ሰምታችሁ ይሆናል . እነርሱ ናቸው የሞስሊሞች ወንድም የሚሆኑት ! አቤት ሙስሊሞቹ ሲጠሏቸው ብታዩ ! ወደ እኛ እየመጡ ለምን እንዚህን አታሳርፉልንም ነው እኮ የሚሉን . " በማለት ተናግሯል . ላይም መረጃ ሰብስበው ጥናት አድርገው አይደለም የተናገሩት . የተወሰኑ ሙስሊም ጓደኞቻቸው ጋር በጉዳዩ ላይ እውርተው ሊሆን ይችላል ; ነገር ግን በጣት የሚቆጠሩ ሙስሊሞች በዚህ ጉዳይ ላይ ያላቸውን ሀሳብ ማወቅና በብዙ ሚሊዮን የሚገመቱ ሙስሊሞች ለሰማያዊ ያላቸውን አመለካከት ማወቅ የተለያየ ነገር ነው .

5 . ስለሀብት ክፍፍል እና ስለኢህአዴግ ርዕዮተ ዓለም

ስለሀብት ክፍፍል ሲናገሩ ደግሞ " በአለም አንደኛ ፍትሀዊት ሀገር ዶብብ ኮርያ ስትሆን ; ኢትዮጵያ ደግሞ ሁለተኛ ናት ; አሜሪካ ደግሞ የመጨረሻዋ ነች አሉ እንግዲህ አሜረካን በደንብ የምታውቁ መስክሩ ; ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ሁኔታ እንኳ በቅርብ እናውቀዋለን ;ምስክር መጥራት የሚያስፈልገን ነገር አይደለም አቦይ ስብሀት ስለኢህአዴግ ርዕዮተ ዓለም ሲናገሩ ; . " ኢህአዴግ ቀኝ ዘምም ግራ ዘመምም አይደለም ; ' sentrums ' ነው ' pragmatisk ' ነው " . አሉ አቶ ልደቱ አያሌው " ሶስተኛ አማራጭ " የሚሉትም ይሄ " sentrums " የሚባለውን በሌበራል ዴሞክራሲ ውስጥ የሚመደብ ርዕዮተ ዓለም ነው . ማንም ሰው ወይም ፓርቲ በቀኝ አክራሪነት ወይም በግራ አክራነት ላለመመደብ በስም " sentrums " መባለን ይፈልጋል . እንደ እውነቱ ከሆነ ግን በእኛ ሀገር በትክክል " sentrums " ሊባሉ የሚችሉ ፓርቲዎች ያሉ አይመስለኝም . በፓርቲው ውስጥ ወደ ቀኝ ጥግ የመሄድ ዝንባሌ እንዳለ ሆኖ በፕሮግራም ደረጃ ወደ " sentrums " የሚጠጋ አቋም ያለው አንድነት ፓርቲ ብቻ ይመስለኛል . ሌላው ሁሉ አንድም በቀኝ , አንድም በግራ የሚመደብ ነው . የኢህአዴግ የሚጠጋ አቋም ያለው አንድነት ፓርቲ ብቻ ይመስለኛል . ሌላው ሁሉ አንድም በቀኝ , አንድም በግራ የሚመደብ ነው . የኢህአዴግ እንኳ ግራ ዘመምም ለመሆኑ ክርክር ውስጥም የሚገባ አይደለም .አቦይ ስብሀት ወደ ጫካ ሲገቡ እድሜያቸው ሰላሳ ዘጠኝ እንደነበረ ራሳቸው በዚያው መድረክ ላይ የተናገሩ ሲሆን አስራ ሰባት ዓመት በትግል 23 ዓመት ደግሞ በስልጣን የቆዩ ከመሆናቸው አንፃር አሁን የሰባ ዘጠኝ ዓመት አዛውንት ናቸው ማለት ነው . ነገር ግን አሁንም ጠንካራ እንደሆኑ ታዝቤያለሁ ; . የዓይን መነፅር እንኳ ሳያድርጉ ነው ሲንቀሳቀሱ የነበረው ነገር ግን አነጋገራቸው ሁሉም አይቶ እንዳሳለፈ ሰው ሆኖ አላገኘሁትም ; ይልቅ ገና የፖለቲካ ስሜቱ እንዳልነበረደለት ጎረምሳ ነው በትዕቢትና በማን አህሎኝነት ሲናገሩ የነበሩት . በተለይ ስለተቃዋሚዎች ሲናገሩ ያላቸውን ጥላቻ በግልፅ ያስታውቅ ነበር . ጥላቻ በዚህ ዕድሜ በጣምም ጥሩ አይደለም::

በጋዜጠኛርዕዮት አለሙ ጉዳይ… የፍርድ ብይኑ ለዳኛው በጽሁፍ እንደተሰጠው ተጋለጠ!!


EMF=ርዕዮት አለሙ ጋዜጠኛ ናት። ሆኖም የኢህአዴግ ስርአት ወጣቷን ጋዜጠኛ “አሸባሪ” በማለት ክስ ከመሰረቱባት በኋላ፤ የ14 አመት እስራት ፈርደውባታል። ይህ ብይን እንደተሰጠ… የፖለቲካ ውሳኔ እንጂ የዳኞች ውሳኔ እንዳልሆነ ውስጥ ውስጡን ሲወራ ነበር። ይህ ወሬ እውነት መሆኑን የሚያረጋግጡ መረጃዎች እየተገኙ መሆናቸውን በተለይ የቤተሰብ ምንጮች ገልጸዋል።

qqየጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ታናሽ እህት እንዳሳወቀችው ከሆነ፡ “በዚህ ሂደት ያገኘኋቸው ሁለት ማስረጃዎች አሉ፡፡ አንደኛው በዳኛው የተነበበው የጥፋተኝነት ውሳኔ የእጅ ጽሁፍ ሲሆን ሁለተኛው የዳኛው የእጅ ጽሁፍ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ማስረጃዎች በእርግጥም የጥፋተኝነት ውሳኔው በዳኛው እንዳልተጻፈ የሚያረጋግጡ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ” ብላለች።

አሁን ብዙዎችን እያነጋገረ ያለው፤ “ከችሎቱ ጀርባ ያለው ድብቅ ዳኛ ማነው?” የሚለው ይሆናል። ይህ በ’ጅ ጽሁፍ ተጽፎ የተሰጠ ብይን የማን እጅ ጽሁፍ ይሆን? ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ላይ ብይን በተሰጠበት ወቅት፤ አቶ መለስ በህይወት ነበሩ… የሳቸው ይሆን? ወይንስ የሽመልስ ከማል እጅ ጽሁፍ ነው?

ህዝቡ በዚህ ጉዳይ የራሱን ትዝብት እንዲወስድ፤ በተለይም የፍርድ ውሳኔው ጸሃፊው ማን እንደነበር ለማወቅ ይህ ደብዳቤ ይፋ ይሆናል። ይህ መረጃ ለህዝብ ይፋ የሚሆነው ጋዜጠኛ ርዕዮት የታሰረችበት 30ኛ ወር በታስቦ በሚልበት፤ ታህሳስ 14 2006 ዓ.ም መሆኑ ታውቋል

ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ጻፉ ክንፉ አሰፋ


ፀሃይ አሳታሚ ድርጅት በታኅሣሥ 16, 2006 ዓ/ም (Dec. 25, 2013) የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩትን የሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስን ‘እኛና አብዮቱ’ የሚል
መጽሃፍ ለገበያ እንደሚያበቃ አስታወቀ። ሻምበል ፍቅረሥላሴ እንደ ደርግ አባልነታቸው በጋራ ያመኑበትን፣ የተማከሩትን፣ የወሰኑትን፣ የሰሩትን፣ የገጠማቸውንና በቅርብ በዓይን ምስክርነት ያዩትን ተንትነው በ‘እኛና አብዮቱ’ ያስነብቡናል። የራሳቸውን ዕይታ ያካፍሉናል።
9781599070780-Perfect.indd
ልጅ ሆነን አንድ አባባል እሰማ ነበር።"አበላል እንደ ደርግ አባል። አለባበስ እንደ ፍቅረሥላሴ ወግደረስ!" - የሚል። በተለይ በኔ ትውልድ ያለን ሰዎች፣ ከዚህ ውጭ ስለኝህ ሰው የምናውቀው ብዙም ነገር አልነበረም። ግና እኝህ ሰው በልባቸው መክሊት ለአመታት የቋጠሩትን መረጃ ጀባ ሲሉን፤”... አጻጻፍም እንደ ፍቅረሥላሴ ወግደረስ" የሚያሰኝ ሆኖ አገኘሁት።
ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ለአስራ አምስት ዓመታት አብዮቱን ሲመሩ ቆይተው ወደ መጨረሻው ከሥልጣን በጡረታ ስም እንዲሰናበቱ ተደርገዋል። ደርግን በጣለው በወያኔ
መንግሥትም ለ፳ ዓመታት ታስረው፣ የሞት ፍርድ የተበየነባቸውና በመጨረሻ ፍርዱ ወደ ዕድሜ ልክ ተዛውሮላቸው ከእሥር ቤት በአመክሮ የወጡ ግለሰብ ናቸው።
ጸሃፊው በድራማ መልክ በመጽሃፋቸው ካሰፈሩዋቸው እውነታዎችና ግለ-ሂሶች ውስጥ አንዳንዶቹን ለአንባቢያን ማካፈሉ አይከፋም። ደርጎች መፈንቅለ መንግስት አድርገው ሲያበቁ ቀዳማዊ ሃይለስላሴ ዘንድ ቀርበው ከንጉሱ የገጠማቸውን አስገራሚ ምላሽ ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ በመጽሃፋቸው እንዲህ ሲሉ አስፍረዋል።
የፖለቲካ እሥረኞች በሙሉ እንዲፊቱ የሚለው ጥያቄ እንደተነበበ ንጉሡ ጣልቃ ገብተው “ለመሆኑ የፖለቲካ እሥረኞቹ እነማን ናቸው?” የሚል ጥያቄ አቀረቡ። “በእርግጥ የምናውቃቸው የፖለቲካ እሥረኞች ባይኖሩም ማንኛውም የፖለቲካ እሥረኛ እንዲፈታ ነው የምንጠይቀው” አሉ ሻለቃ ተስፋዬ ገብረኪዳን። ንጉሡ ራሳቸውን ነቅነቅ አድርገው ጽሑፉን የሚያነበውን የደርግ አባል እየተመለከቱ “አልገባችሁም!” ብለው ዝም አሉ። በእርግጥም አልገባንም። ተማሪዎችና የተለየ ዓላማ የነበራቸው የተማሩ ሰዎች የሰነዘሩትን መፈክር ብቻ ነበር ይዘን ንጉሡ ፊት የቀረብነው። በፖለቲካ እሥረኝነት ስም በከፍተኛ ደረጃ ለጣሊያን ወራሪ መንግሥት በባንዳነት አድረው አገራችንን የወጉ፣ ለቅኝ ተገዥነትም የዳረጉትን እንደ ኃይለሥላሴ ጉግሳ ያሉ ወንጀለኞች የፖለቲካ እሥረኞች ተብለው ከግዞትና ከእሥር ቤት አስወጥተን እንደ ጀግና ራሳቸውን እንዲቆጥሩ አደረግናቸው።
የነ ጄነራል ተፈሪ በንቲ ጉዳይን አስመልክቶ የሰፈረው ታሪክ ደግሞ እንዲህ ይነበባል። “በሊቀመንበርነት ስብሰባውን የሚመሩት ጄነራል ተፈሪ 'የቋሚ ኮሚቴው'በዛሬው ቀን የሚወያይበትን ጉዳይ አስመልክቶ የመቶ አለቃ ዓለማየሁ የደርጉ ዋና ፀሐፊ ይገልጽልናል' ብለው ስብሰባው መጀመሩን ካበሰሩ በኋላ ዓለማየሁ በአጀንዳው ላይ አጭር ገለጣ ማድረግ ሲጀምር ስልክ ተደወለ። ስልኩ ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ አጠገብ ስለነበር ወዲያው ቅጭል እንዳለ መነጋገሪያውን በማንሳት ሃሎ አሉ።
ከሌላው ጫፍ ማን እንደደወለ አላወቀንም። በኋላ እንደታወቀው ሌ/ኮሎኔል ዳንኤል ነበር የደወለው።
ምን እንደተነጋገሩ አልተሰማም። ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ብቻ “እሺ እሺ” ብለው ስልኩን ዘጉት። ስልኩን እንደዘጉ “ይቅርታ ስልኩ የተደወለው ከጎንደር ነው። ጎንደር ውስጥ ችግር አለ። እናንተ ቀጥሉ” ብለው ከጀርባቸው ባለው በር በኩል ውልቅ አሉ። በዚህን ጊዜ ዓለማየሁና ሞገስ ጥርጣሬ የገባቸው መሰለ።
ዓለማየሁ ንግግሩን አቋርጦ በመስኮት በኩል ውጭ ውጭዉን መመልከት ጀመረ። ዓይኖቹ አላርፍ አሉ። ግራና ቀኝ ይመለከታል። አጠገቡ ያሉትን ሰዎች ሁሉ በጥርጣሬ ተመለከተ። ሻምበል ሞገስም በር በሩን ይመለከታል። ከአሁን አሁን አንድ ችግር ይከሰታል የሚል ፍርሃት ያደረበት ይመስላል። ሁሉም የኢሕአፓ አባላትና ደጋፊዎች ፈርተዋል። እንደፈሩት አልቀረም ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ከወጡ ሁለት ደቂቃ እንኳን አልሞላም ከበስተጀርባ ባለው ኮሪደር የወታደሮችን እርምጃ ሰማን። ወታደሮች ሲንቀሳቀሱ በፊት ለፊታችን ባሉት መስኮቶች በኩል ተመለከትን። በዚህን ጊዜ ፍስሐ ደስታ “ተከብበናል” አለ። ወዲያው ሁለቱም በሮች በኃይል ተበረገዱ። ሁላችንም ደነገጥን፣ ቀልባችን ተገፈፈ፣ እጢአችንም የወደቀ መሰለን። ድርቅ ብለን በተቀመጥንበት ቀረን።...
ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ሰለ ልጅ ሚካኤልን አስተዋይነት ሲያስታውሱ እንዲህ የሚል ግለሂስም ያስነብቡናል። እኛ በችኮላ ውሳኔ መስጠታችን፣ ሕዝቡን በደንብ አለማወቃችን፣ ሰፊ የሕዝብ አመራር ልምድ ማጣታችን፣ የአገርና የውጭውን ፖለቲካ ውስብሰባዊ ግንኙነት አለመገንዘባችን፣ የመንግሥትን አሠራር ደንብና ሥርዓት አለመረዳታችን፣ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ጥመርታዊ ግንኙነትን መመልከት አለመቻላችን፣ የተለያየ ገንቢም ሆነ አፍራሽ ተልዕኮ ያላቸው ኃይሎች ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩብ ያለማጤናችን፣ በየዋህነትና በቅንነት ብቻ እንደምንሠራ በመገንዘባቸው ሊሆን ይችላል ልጅ ሚካኤል ከእኛ ጋር መቆየት የሚችሉት ለአጭር ጊዜ ብቻ እንደሚሆን የጠቆሙት...
በወቅቱ ስለ ህዝቡ የእርስ በርስ መጨካከንና መወነጃጀል ባሰፈሩት ክፍል ውስጥ እንዲህ የሚል ታሪክ እናገኛለን።
..የሥራ ዕድገት የተከለከለ፣ በሌብነትም ሆነ በስካር ወይም በሌላ ጥፋት የተቀጣ፣ በግል ጉዳይም ሆነ በመንግሥት ሥራ ከአለቃው ጋር የተጣላ፣ በአጋጣሚው ተጠቅሞ አዲስ ሹመት ወይንም ዕድገት
ለማግኘት የሚፈልግ ሁሉ ጠቋሚ፣ ወንጃይ፣ ከሳሽ፣ ተበዳይ ነው። የተወሰነ ጥቅም ለማግኘት ወይም ሌላውን ለመጉዳት ብለው “ኢትዮጵያ ትቅደምን ይቃወማል፣ ከታሠሩት ባለሥልጣናት ወይም ሚኒስትሮች የቅርብ ዝምድና አለው። ስለሆነም ሥራ ይበድላል፣ ሠራተኛውን ያጉላላል፣ ውሳኔ አይሰጥም” በማለት አለቆቻቸውን የሚከሱ፣ የሚወነጅሉ በርካታ ናቸው። ለደርግ አባላት ቤታቸው ድረስ በመሄድ በማስረጃ የተደገፈ ቢሆንም ባይሆንም ተቆርቋሪ በመምሰል የክስ ማመልከቻ የሚያቀርቡም ነበሩ። እንታሠራለን ብለው በፍርሃት
የተደበቁ ባለሥልጣናትን የቅርብ ዘመዶቻቸው ወይም አሽከሮቻቸው ወይም ጎረቤቶቻቸው ደርግ ጽሕፈት ቤት ድረስ በመምጣት ያጋልጧቸው ነበር። የመሥሪያ ቤቶችን ሰነዶች ፎቶ ኮፒ በማድረግ ወይም ሰነዱን እንዳለ ከፋይሉ አውጥተው በማቅረብ “በመንግሥት ንብረት፣ ሀብት ወይንም ገንዘብ ላይ አላግባብ ተወስኗል” ብለው ጥቆማና መረጃ የሚያቀርቡም ነበሩ።
ሠራተኞች አሠሪዎቻቸውን ይከሳሉ፣ ይወነጅላሉ። ገበሬዎች ለዘመናት በደል አደረሱብን የሚሏቸውን የአካባቢ ባለሥልጣናት ይወነጅላሉ። ውንጀላው በርካታ ነው።
አሽከሮች፣ ዘበኞች፣ ገረዶች... መረጃ ይሰጣሉ፣ ይጠቁማሉ። የተደበቀ የጦር መሣሪያ፣ የተደበቀ ገንዘብ፣ ወደሌላ ቦታ የተወሰደ ወይም የሸሸ ሀብት እንዳለም የሚጠቁሙን እነሱ ናቸው።
በአንድ ቦታ በርከት ያሉ ሰዎች ተሰብስበው ምሽት ከአሳላፉ “ሲያድሙ ነበር” ብለው ከነስም ዝርዝራቸው መረጃውን ደርግ ጽሕፈት ቤት ድረስ ያመጣሉ። “እኛ እስከዛሬ የበይ ተመልካች ነበርን ዛሬ ዕድሜ ለእናንተ እንጀራ ሊወጣልን ነው! ከእናንተ ጎን ተሰልፈን አቆርቋዦቹን እንታገላለን! በማንኛውም ጊዜ ትዕዛዝ ብትሰጡን ለመፈጸም ዝግጁ ነን!” እያሉ ታማኝነታቸውንና ተባባሪነታቸውን የሚገልጡም ብዙዎች ነበሩ። በጣም የሚያስደንቀው አባቶቻቸውን፣ ልጆቻቸውን፣ ወንድሞቻቸውን፣ እህቶቻቸውን፣ ባሎቻቸውን፣ ሚስቶቻቸውን በመክሰስ፣ በመወንጀል፣ በማጋለጥ፣ በመጠቆም ብሎም በማሳሰር ጉዳት ያደረሱ በርካቶች መሆናቸው ነው።
እንግዲህ ስለ አዲሱ ‘እኛና አብዮቱ’ መጽሃፍ ይህንን ካልኩ ቀሪውን ለአንባቢ መተው ይበጃል። ሁሉም ሰው መጽሃፉን አንብቦ የራሱን ፍርድ ይስጥ።
ህይወት በሩጫ ትመሰላለች። የተፈጥሮ ህግጋት ነውና የሰው ልጅ እስትንፋሱ እስኪቋረጥ ይሮጣል። ከዚያም ሩጫውን ይጨርሳል። ሩጫውን ሳይጨርስ በልቡ ቋጥኝ የያዘውን እምቅ ቋጠሮ የሚተነፍስ ደግሞ እድለኛ ነው። በአንጻሩ ደግሞ በአእምሮው የቋጠረውን የእውቀት ምስጢር ሳያካፍል የሚያልፍ ሁሉ ያሳዝናል።
ያለውን የወረወረ ንፉግ አይደለምና መንቀፍም ካለብን የሚወረውረውን ሳይሆን የማይወረውረውን ነው። መተቸት ካለብነም ሃሳቡን እንጂ ግለሰቡን ባይሆን ይመረጣል። በሃሳብ ላይ መወያየትና መተሻሸት ደግሞ አዋቂነት ነው።
በመጨረሻም የመጽሃፉ አርታኢ ኤልያስ ወንድሙ በመግቢያው ላይ ባሰፈረው መልእክት ጽሁፌን ልቋጭ። የተማረ፣ ያወቀና ያደገ ትውልድና ዜጋ ምልክቱ የተጻፈን ማንበቡ፣ ያነበበውን ማብላላቱና ካነበበው ውስጥ ስንዴውን ከእንክርዳዱ መለየቱ ሲሆን፤ እራሱም አስተውሎና አገናዝቦ መጻፉ ደግሞ መማሩን ብቻ ሳይሆን መመራመሩንና ማወቁን የሚያሳይ ታላቅ ተግባር ነው። ለዚህም ደግሞ ግላዊ ነጻነት ያስፈልገዋልና ጫንቃው ላይ ያሉትን ግላዊና ታሪካዊ ቀንበሮች የሰበረ ነጻ ሰው መሆን ይጠበቅበታል። ትምህርትና ዕውቀት አስተዋይነትንና ጥልቀትን ከራስ በላይ ለትውልድ አሳቢነትን የሚያመለክት ታላቅ ኃላፊነት ነው። ለዚህም እንደ ትናንቱ ‘የተማረ ይግደለን’ ሳይሆን፤ የተማረ ያስተምረን፣ ያስተዳድረን ብሎም ይምራን በምንልበት ዘመን ከምናነብበው ውስጥ ያልተስማማንበትን በጨዋነት የመቃወም፣ የፈቀድነውን እንደ ስሜታችን የመደገፍና ተሳሳተ የምንለውን ለእርማት መጠቆም ግላዊ መብታችን
ነው።...
* ፀሃይ አሳታሚ ድርጅት ከዚህ በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያምን፣ የቀድሞውን የህወሃት መሪ ዶ/ር አረጋዊ በርሄን፣ የቀድሞውን የኢህአፓን አመራር አባል የዶ/ር መላኩ ገኝን፣ የቀድሞው ሚንስትር የአቶ ተካልኝ ገዳሙን መጽሃፍትና ከስልሳ በላይ የሆኑ በኢትዮጵያ ታሪክና ጥናት ላይ ያተኮሩ መጽሃፍትን ማሳታሙ ይታወሳል። ‘እኛና አብዮቱ’ የሚለው ይህ አዲስ መጽሃፍ በwww.tsehaipublishers.com ድረገጽና በቀርቡ በየሱቁ አንደሚገኝ ከሎስ አንጀነሰ
የደረሰን ዘገባ አስታውቋል። ሁላችንም ገዘተን እናንብብ።

100 ኢትዮጵያዊያን ኢሚግሬሽን እስር ቤት በር ላይ ወድቀዋል፡፡በግሩም ተ/ሀይማኖት

አንዲት ኢትዮጵዊን አንድ ሀበሻ አሳሰራት ብለው ነገሩኝ፡፡ ያ አሳሰረ የተበለውን ሰው ፈልጌ ለማናገር መፍትሄ ለማግኘት እንጂ እስር ቤት ሄጄ እሷን ማየት አላሰብኩም፡፡ ምክንያቴ ከእስር የምትወጣበትን መንገድ መፈለግ ነበር፡፡ በመሀል ልጅቱን ለመጠየቅ ወደ እስር ቤት ከሄዱት መካከል ነብዩ ተስፋዬ የሚባለው ልጅ ደወለልኝ፡፡ 
‹‹..እስር ቤት ጊቢ በር ላይ ተኝተዋል፡፡ እስኪ አንዱን አናግረው አለኝ…›› ሞባይል ስልኩን አቀበለው፡፡ ‹‹…ወንድሜ ልብሳችንን ነጥቀው አቃጠሉት፣ ከዚህ በር ላይ ሂዱ ብለው አባረሩን ርቦናል ጠምቶናል…ከነጋ አልበላንም እርቦናል….›› መስማት አልቻልኩም፡፡ ሰሞኑን ባደረብኝ በጤና ችግር ምክንያት አርብ እለት ሄጄ ላያቸው ባለመቻሌ ውስጤን ጸጸት ሸነቆጠው፡፡ ግን ወድጄ አልነበረም፡፡ መንገድ ላይ ቢያመኝ ብዬ በመፍራት ሄለን ገ/እግዚአብሄርን አስከትዬ በቀጥታ በኮንትራት ታክሲ ወደ ኢሚግሬሽን እስር ቤት አመራሁ፡፡ ስደርሰ ባየሁት ነገር ከሚገባው በላይ አዘንኩ፡፡ አነባሁም፡፡ በምን አይነት አለመታደል ነው የተሰነግነው? ምን አይነት እርግማ ነው ያለቀቀን..ምን አይነት ተስፋ ማጣት ነው አሁንም ሳዑዲ አረቢያ ለመሄድ ባህር እያሻገረን ያለው ሁኔታ?፡፡ ምን አይነት መጨካከን ነው እንደካባ የደረብነው፡፡ እነዚህን ልጆች እያየ አልፎ ገብቶ ሌላ ኢትዮጵያዊት ያሳሰረው አለማየሁ አንጀቱ እንዴት ቻለው ስል ራሴን ጠየኩ፡፡ ግን ምላሹ በእየአንዳንዳችን ማንነት ውስጥ የጠፋ እኛነት ሆኖ ነው የታየኝ፡፡

አንጀታቸው እጥፍ ያለ፣ በርሃብ የከሱና የጠቋቆሩ፣ የሚለብሱት የሌላቸው 102 ልጆች እስር ቤት ገብተው ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ፈልገው እሰሩን ቢሉም ጭራሽ ፖሊስ ከቦታው እንዲሄዱ አባረራቸው፡፡ ነፍሳቸውን ለማዳን ሮጡ፡፡ ጥለውት የሮጡትን ልብስ እና በእንደ ብርድ ልብስ የሚጠቀሙበትን ከሰው ያገኙትን ልብስ ሰብስበው ፖሊሶቹ አቃጠሉባቸው፡፡ በዛ አጥንትን በሚሰብር ብርድ እንዲሁ ራቁታቸውን አድረው ጦም ውለው ነው እንግዲህ እኔ የደረስኩት፡፡ ምንስ ባደርግ የተሰመማኝ ሀዘን ከውስጤ ይወጣል፡፡ አማራጭ የለኝም፡፡ ዞሬ የሄድኩበት እና ቆሞ የሚጠብቀኝ ታክሲ ውስጥ ገባሁ፡፡ ሄለን እና ነጅብ በመለቀው ቪዲዬ ላይ ታዩዋቸዋላችሁ እነሱን ይዤ ለ100 ሰው ምግብ ላገኝ የምችልበትን አካባቢ እና ሆቴል ፍለጋ ዳከርኩ፡፡ ተመስገን አግኝቼ መቶ ፉል አዘዝን፡፡ ኩብዝ የሚባለውን ቂጣ ነገር 300 ያህል ገዛሁ፡፡ ይህን ሁሉ የማደርገው ከዚህ ቀድሞ በግሌ ለማደርገው እስረኞችን የማብላት፣ የማልበስ እና የሚያስፈልጓቸውን ነገሮች ማቅረብ እንቅስቃሴ እንዲረዳኝ ብለው ጥቂት ሰዎች ከላኩልኝ የተወሰነውን ከትላንት ወዲያ አርብ ለእስረኞቹ አዘጋጅቼ ልሄድበት ባስቀምጠውም በጤና ችግር ምክንያት አርብ እለት ወደነሱ መሄድ ባለመቻሌ የቀረ ነበር፡፡ ለነገሩ ከስዊድን የኢትዮጵያዊያ ሬድዬ ጋዜጠኞች በኩልም የደረሰኝ ስለነበር ዛሬ እሁድ ታህሳስ 13 ምሳ የማብላት ዝግጅት አዘጋጀሁበት፡፡

2013 prison census, 211 journalists jailed worldwide

pizap_com10_89121895469725131379474868932
Ethiopia: 7
Saleh Idris Gama, Eri-TV
Tesfalidet Kidane Tesfazghi, Eri-TV
Imprisoned: December 2006
Tesfalidet, a producer for Eritrea’s state broadcaster Eri-TV, and Saleh, a cameraman, were arrested in late 2006 on the Kenya-Somalia border during Ethiopia’s invasion of southern Somalia.
The Ethiopian Foreign Ministry first disclosed the detention of the journalists in April 2007, and presented them on state television as part of a group of 41 captured terrorism suspects, according to CPJ research. Though Eritrea often conscripted journalists into military service, the video did not present any evidence linking the journalists to military activity. The ministry pledged to subject some of the suspects to military trials but did not identify them by name. In a September 2011 press conference with exiled Eritrean journalists in Addis Ababa, the late Prime Minister Meles Zenawi said Saleh and Tesfalidet would be freed if investigations determined they were not involved in espionage, according to news reports and journalists who participated in the press conference.
But Tesfalidet and Saleh had not been tried by late 2013, and authorities disclosed no information about legal proceedings against them, according to local journalists. Authorities also did not disclose any information about their health or whereabouts.
Woubshet Taye, Awramba Times
Imprisoned: June 19, 2011
Police arrested Woubshet, deputy editor of the independent weekly Awramba Times, after raiding his home in the capital, Addis Ababa, and confiscating documents, cameras, CDs, and selected copies of the newspaper, according to local journalists. The outlet’s top editor, CPJ International Press Freedom Awardee Dawit Kebede, fled the country in November 2011 in fear of being arrested; the newspaper is published online from exile.
Government spokesman Shimelis Kemal said Woubshet was among several people accused of planning terrorist attacks on infrastructure, telecommunications, and power lines with the support of an unnamed international terrorist group and Ethiopia’s neighbor, Eritrea, according to news reports. In January 2012, a court in Addis Ababasentenced Woubshet to 14 years in prison, news reports said.
CPJ believes Woubshet’s conviction was in reprisal for Awramba Times‘ critical coverage of the government. Prior to his arrest, Woubshet had written a column criticizing what he saw as the ruling party’s tactics of weakening and dividing the media and the opposition, Dawit told CPJ. Woubshet had been targeted in the past. He was detained for a week in November 2005 during the government’s crackdown on news coverage of unrest that followed disputed elections.
In April 2013, authorities transferred Woubshet from Kilinto Prison, outside Addis Ababa, to a detention facility in the town of Ziway, about 83 miles southeast of the capital, according to local journalists and the Awramba Times. Ziway, one Ethiopia’s largest prisons, is a maximum-security jail designed for those convicted of serious offenses, according to local journalists. The authorities did not provide a reason for the transfer. In November, Woubshet was transferred back to Kality prison because he was in poor health, according to local journalists.
Woubshet did not appeal his conviction and applied for a pardon, according to local journalists. In August 2013, the Ethiopian Ministry of Justice rejected the request for a pardon, the Awramba Times reported.
In October 2013, Woubshet was honored with the Free Press Africa Award at the CNN MultiChoice African Journalist Awards in Cape Town, South Africa.
Reeyot Alemu, freelance
Imprisoned: June 21, 2011
Ethiopian security forces arrested Reeyot, a prominent, critical columnist for the leading independent weekly Feteh, at an Addis Ababa high school where she taught English. Authorities raided her home and seized documents and other materials before taking her into custody at the Maekelawi federal detention center.
Ethiopian government spokesman Shimelis Kemal said Reeyot was among several people accused of planning terrorist attacks on infrastructure, telecommunications, and power lines in the country with the support of an unnamed international terrorist group and Ethiopia’s neighbor, Eritrea, according to news reports. Authorities filed terrorism charges against Reeyot in September 2011, according to local journalists.
The High Court sentenced Reeyot in January 2012 to 14 years in prison for planning a terrorist act; possessing property for a terrorist act; and promoting a terrorist act. The conviction was based on emails she had received from pro-opposition discussion groups; reports she had sent to the U.S.-based opposition news site Ethiopian Review; and unspecified money transfers from her bank account, according to court documents reviewed by CPJ.
CPJ believes Reeyot’s conviction is due to columns she wrote that accused authorities of governing by coercion, by (for example) allowing access to economic and educational opportunities only to those who were members of the ruling party, according to CPJ’s review of the translations in 2013. In the last column published before her arrest, she wrote that the ruling party had deluded itself in believing it held the legitimacy of popular support in the way of late Libyan leader Muammar Qaddafi, according to local journalists.
In August 2012, the Supreme Court overturned Reeyot’s conviction on the planning and possession charges, but upheld the charge of promoting terrorism. The court reducedher sentence to five years.
In January 2013, the Ethiopian Court of Cassation, the last resort for legal appeals in Ethiopia, rejected Reeyot’s appeal, according to news reports. She is being held at Kality Prison in Addis Ababa.
In March 2013, prison authorities threatened to place Reeyot in solitary confinement for saying she would publicize the abuse of her rights, according to her lawyer and family members. The same month, the United Nations special rapporteur on torture and other cruel, inhuman, or degrading treatment issued a report that determined Reeyot’s rights under the U.N. Convention Against Torture had been violated by the government’s failure to respond to allegations of her ill treatment. Reeyot’s health had deteriorated while she was held in pretrial detention, reports said.
In April 2013, Reeyot won the 2013 UNESCO-Guillermo Cano World Press Freedom Prize in recognition of her courage and commitment to freedom of expression.
In September 2013, prison officials limitedReeyot’s visitors to her parents, denying visits from her fiancé, relatives, and friends. The journalist waged a four-day hunger strike in protest. Kemal said that Reeyot was being disciplined for violating prison laws, but did not elaborate, according to news reports.
Eskinder Nega, freelance
Imprisoned: September 14, 2011
Ethiopian security forces arrested Eskinder, a prominent online columnist and former publisher and editor of now-shuttered newspapers, on vague accusations of involvement in a terrorism plot. The arrest came five days after Eskinder published acolumn on the U.S.-based news website EthioMedia that criticized the government for misusing the country’s sweeping anti-terrorism law to jail prominent journalists and dissident intellectuals.
Shortly after Eskinder’s arrest, state television portrayed the journalist as a spy for “foreign forces” and accused him of having links with the banned opposition movement Ginbot 7, which the Ethiopian government designated a terrorist entity. In an interviewwith Agence France-Presse, government spokesman Shimelis Kemal accused the detainee of plotting “a series of terrorist acts that would likely wreak havoc.” Eskinder consistently proclaimed his innocence, but was convicted on the basis of a video of a public town hall meeting in which he discussed the possibility of a popular uprising in Ethiopia if the ruling party did not deliver democratic reform, according to reports.
In July 2012, a federal high court judge in Addis Ababa sentenced Eskinder to an 18-year prison sentence, according to local journalists and news reports. Five exiled journalists were convicted in absentia at the same time.
Also in 2012, a U.N. panel found that Eskinder’s imprisonment came as “a result of his peaceful exercise of the right to freedom of expression,” according to a report publishedin April 2013.
In May 2013, Ethiopia’s Supreme Court rejected an appeal and upheld the sentence.
CPJ believes the charges are part of a pattern of government persecution of Eskinder in reprisal for his coverage. In 2011, police detained Eskinder and threatened him in connection with his online columns that drew comparisons between the Egyptian uprising and Ethiopia’s 2005 pro-democracy protests, according to news reports. His coverage of the Ethiopian government’s repression of the 2005 protests landed him in jail for 17 months on anti-state charges at the time. After his release in 2007, authorities banned his newspapers and denied him licenses to start new ones. He was first arrested in September 1993 in connection with his articles in the Amharic weeklyEthiopis, one of the country’s first independent newspapers, about the government’s crackdown on dissent in Western Ethiopia, according to CPJ research.
Eskinder was being held at Kality Prison in Addis Ababa, with restricted visitation rights, in late 2013.
Yusuf Getachew, Ye Muslimoch Guday
Imprisoned: July 20, 2012
Police officers raided the Addis Ababa home of Yusuf, editor of the now-defunct Ye Muslimoch Guday (Muslim Affairs), as part of a broad crackdown on journalists and news outlets reporting on protests staged by Ethiopian Muslims. The Muslims were demonstrating against government policies they said interfered with their religious freedom. The government sought to link the protesters to Islamist extremists and tried to suppress coverage by arresting several local and international journalists and forcing publications to close down, according to local journalists and news reports.
After Yusuf’s arrest, other Ye Muslimoch Guday journalists went into hiding, and the publication ceased operations, local journalists told CPJ.
Yusuf spent weeks in pre-trial custody at the Maekelawi federal detention center without access to his family and limited contact with his lawyer, according to local journalists.
In October 2012, he was formally charged under the 2009 Anti-Terrorism Law with plotting acts of “terrorism [and] intending to advance a political, religious, or ideological cause,” according to local journalists. Yusuf told the court he had been beaten in custody, local journalists told CPJ.
Prosecutors accused Yusuf of inciting violence in columns in Ye Muslimoch Guday by alleging that the government-appointed Supreme Council for Muslim Affairs was corrupt and lacked legitimacy, according to local journalists and court documents obtained by CPJ. The prosecution also used as evidence Yusuf’s CDs with Islamic teachings even though these were widely available in markets, according to local journalists.
The editor is being held at Kality Prison in Addis Ababa. The trial was ongoing in late 2013.
Solomon Kebede, Ye Muslimoch Guday
Imprisoned: January 17, 2013
Police arrested the managing director of the now-defunct Ye Muslimoch Guday (Muslim Affairs), as part of a broad crackdown on journalists and news outlets reporting on peaceful protests staged by Ethiopian Muslims against government policies they said interfered with their religious freedom. The government sought to link the protesters to Islamist extremists and attempted to suppress coverage by arresting several local andinternational journalists and forcing publications to close down, according to local journalists and news reports.
Solomon was held at the Maekelawi federal detention center for weeks without access to his family and with limited contact with his lawyer, according to local journalists.
A few weeks after his arrest, Solomon was formally charged under the Ethiopian anti-terrorism law, according to local journalists. Authorities have not disclosed any evidence against him. His case was ongoing in late 2013, according to a human rights lawyer familiar with matter.

“438 Days” in Ethiopian custody – a book by Swedish Journalists

“438 Days” in Ethiopian custody – a book by Swedish Journalists
By: Yusuf M Hasan (somalilandsun)
Somalilandsun – The Authors of “438 DAGAR” Martin Schibbye, and Johan Persson, which is a book detailing their “438 Days” in Ethiopian custody and related experiences have now turned to exposing the ills they perceive to be ongoing in the Ogaden Region.
In an exclusive interview with journalist Mohamed Farah of Ogadentoday Press the two Swedish scribes say their motivation to pursue information on the region some refer to as “Ethiopia’s Darfur” or “Africa’s Palestine” by the burning desire to bring to light inhuman activities that were known but craftily what hidden from the International Community.
Describing their arrest by Ethiopian Counterinsurgency forces operating in the Ogaden region against the Ogaden National Liberation Front-ONLF that led to the 438 Days” in Custody Journalist Schibbye said that 150 soldiers who had been pursuing them for some time opened sporadic gunfire injuring him on the shoulder while colleague Johan got hit in the arm
Though the two faced extreme torture especially lack of medical attention, the counter insurgency forces viewed them as hostile elements geared towards disruption of national security since they, the Swede journalists undertook their coverage under guidance of and accompanied by members of ONLF, an armed group the Ethiopian government considers rebellious thence outlawed.
Below are the verbatim excerpts of the interview
Ogadentoday Press: Welcome to Ogadentoday Press
Martin Schibbye: Thank Very Much
Ogadentoday Press: What makes you to travel into Ogaden and put yourself at risk?
Martin Schibbye: Despite, many reports written about the conflicts in the Ogaden, no-one set foot in the oil-fields to report on and that drove us to try and use our legs to see with our own eyes the impacts of the Oil-Industry rather than googling to cover the story. The only conventional way into the area is to make an official visit, stage managed by the Ethiopian regime, pausing for a few hours in some well‐run hospital. These things are organised at regular intervals. At some point, you have to make a choice as a journalist. Either you produce a text in which Ethiopia claims there is peace in Ogaden, while the separatist movement, ONLF, insists there is a state of war. And you’re satisfied with that. Or you try to find out what’s true. Which of the perspectives are accurate. Either refugees were tortured by the Ethiopian army, or they weren’t. Either there is conflict in the region – or not. It shouldn’t be a matter of opinion. That is why we have to go into, so we can see with our own eyes what the consequences are of the activities of the international oil companies
Ogadentoday Press: Did you have a chance to meet and interview the local Ogadenis inside Ogaden region?
Martin Schibbye: No, not really, the conflict level is high and the area is militarized .We passed through an empty village that its residents fled due to the conflict. We pass abandoned huts, and meet an elderly man wandering the desert who says his village was burnt to the ground and everyone was killed. He planned to flee to Dadaab. We also make a long interview with the commander of the ONLF group that is guiding us about why they fight and their views on foreign oil companies. Because of the heavy fighting in the area that we passed through the Ethiopian army detected, followed and ambushed us.
Ogadentoday Press: When did you fall into the hands of the notorious Liyu Police militia? And how did they treat you?
Martin Schibbye: On June 30, about 150 Ethiopian soldiers attacked and opened fire on us I got hit in the shoulder and Johan got hit in the arm. Then, I shouted: “Media! Media! International Press!” After we were arrested, we were not given medical care, a chance to contact our Embassy, or taken to a court but instead kept us in the desert for four days. It was the longest and the worst days that I have ever experienced in my life. The army started to make a mockumentary about what has happened and they brought in military journalists and gave us clean clothes. We were told to co-operate or we would be killed. To make us cooperate they arranged a mock execution. Driving us around to different locations to act like a Steven Spielbergy film. The film’s director was the vice-president, Abdullaahi Yuusuf Weerar, conversing with the regional president, Abdi Mohamoud Omar by phone.
Ogadentoday Press: Were you imprisoned in one of Ogaden jails?
Martin Schibbye: We spent a couple of nights at the police station in the regional prison of Jigjiga but then we were taken to Maekalawi prison in Addis Ababa. In the beginning, we thought that if we could prove that we were journalists we would go free, but the opposite happened. We were sentenced and charged as terrorists because of being journalists. They made an assessment. At one hand international criticism on the other hand to scare away both foreign journalists and the local ones. Meles Zenawi was on top of our case from day one and wanted to make an example.
In detention we realized that we were not alone as all the cells from right to left where crowded with politicians and Journalists charged with terrorism. It was obvious that we were in the middle of crackdown because of Ethiopia’s anti-terrorism law restricted freedom of expression and used it as a tool to crackdown on dissidents.
Ogadentoday Press: How do you describe Kality jail to people that have never been in it?
Martin Schibbye: Its impossible. Its eight zones with 800-1000 prisoners in every zone. Basically its crowded like a music festival, but without beer, without music and with a lot of soldiers with guns. It was 200% overcrowded, hot, dusty, lack of water, full of rats and fleas and many people were very sick among them, people with HIV and tuberculosis infections. But the conditions were not as significant as the other inmates. What is concerning is not the condition but who they put in there: Journalists and political opposition figures. There was also something else in Kality. A friendship between prisoners. The first word I learned in Amharic was “nubla”, “come and eat”. We hade a lot of support from fellow prisoners.
Ogadentoday Press: Ethiopia government regards jailed Journalists in Kality as terrorists, do you agree?
Martin Schibbye: No, we have been accused of the same things, we had been to the same prison and had the same sentences-but that is where the parallel ends: Eskinder Nega, Woubshet Taye, and Reeyot Alemu and many others still there. Only me and Johan are free.
All these young Ethiopian journalists faced a tough choice. They are intelligent, and well-educated .They could have chosen an easy life. They could have chosen another profession, but the love for the truth to their country for their human being made them journalists. They stayed and continued to write, and that decision brought them to Kality.
With nine detained journalists left in Kality, Ethiopia today is one of the leading countries in the world when it comes to imprisoning members of the press. Repression of the media has also made the country a world leader when it comes to running journalists out of the country.
Ogadentoday Press: Do you believe that your book for “438 days” can expose both the plights of Ogaden people and Prisoners of conscience in Ethiopia?
Martin Schibbye: Since our release I have often been asked if the attention helps the imprisoned or not. My answer is that it is far more important than food and water. When you’re locked up as a prisoner of conscience, the greatest fear is to be forgotten. The support from the outside is what keep you going and international coverage does provide a certain level of protection. Prison guards and administrators will think twice because they know the world is watching. But we should also be aware of that the arrest of me and Johan Persson made evident the damage to its reputation the Ethiopian government was willing to accept in its effort to silence independent reporters.
One positive outcome of our book and a newly released documentaryfilm based on material smuggled out by Abdulahi Hussein (a former adviser to the state president Abdi Muhamud Omar and now a refugee in Sweden) is that The International Public Prosecutors Office in Sweden has decided to start an investigation of suspected war crimes against a number of identified politicians and military personel in the Ethiopian region of Ogaden. Pointed out are the regional president Abdi Muhamud Omar and the vice president Abdulahi Werer. I hope that the ones responsible for the terrible atrocities can be held accountable.
As long as Ethiopia can commit crimes, jail journalists and get away with it, it is a cheap and easy way of censorship. To jail a journalist should be regarded as a crime against humanity. But in this regard, I don’t put my hopes to international pressure. For now, the jailed journalists are nothing more than “an irritant” in the diplomatic world. It’s business as usual.
I put my hope in the young generation which I shared the concrete floor with in Kality. Despite, the daily propaganda on the Ethiopian state television, ETV, very few in Kality regards the jailed journalists as terrorists.
I have an unquestioning faith in Ethiopia’s young people.
Ogadentoday Press: Thank you so much, Martin Schibbye for your time.

ከወያኔ ክፋትና እብሪት እንጂ ፍትህ አይጠበቅም

26351fb59e29fb0a1375427042
December 19, 2013
ወያኔ ባለፉት ሃያ ሁለት አመታት የአገራችንን የፍትህ ተቋሞች አንዴ አንደ ቂም መበቀያ ሌላ ግዜ ደግሞ እንደ ማጥቂያ መሳሪያ እየተጠቀመባቸዉ የፖለቲካ ተቀናቃኞቹንና ጥርስ የነከሰባቸዉን የህብረተሰብ አባላት እያሰረ፤ እያሳደደና እየገደለ ከርሞ ዛሬ ላይ ደርሷል። በተለይ ከግንቦት 1997ቱ ምርጫ በኋላ ወያኔ ብዕርና ወረቀት ይዘዉ በሃሳብና በአመክኖ የታገሉትን ሰላማዊ ዜጎች “ሽብርተኞች”፤ ድምጻችን ይሰማ ብለዉ የመብትና የነጻነት ጥያቄ አንግበዉ በሰላማዊ መንገድ የታገሉትን ኢትዮጵያዉያን የእስልምና እምነት ተከታዮች ደግሞ “አክራሪዎች” እያለ ፍርድ ቤት በማቅረብ በፍትህ ተቋሞች በኩል የፖለቲካ ዉሳኔ በማሳለፍ ሠላማዊ ዜጎችን ለረጂም ግዜ እስርና እንግልት ዳርጓል።
ወያኔ ለኢትዮጵያና ለዜጎቿ ደንታ የሌለዉ እና ከስህተቱ የማይማር የግብዞችና የዘረኞች ስብስብ ስለሆነ አሁንም የአገሪቱን የፍትህ ተቋሞች እንደ ማጥቂያ መሳሪያ እየተጠቀመ የኢትዮጵያን ህዝብ በፍርሃት ጨለማ ዉስጥ ሸብቦ እየገዛ ለመኖር የቆረጠ ይመስላል። ባለፈዉ ሳምንት አጋማሽ ላይ የወያኔ አገዛዝ ከአንድ አመት ተኩል በላይ እስር ቤት ዉስጥ አጉሮ ያቆያቸዉን የድምጻችን ይሰማ መሪዎች ከፊሎቹን በነፃ ተለቅቀዋል የሚል ከፊሎቹን ደግሞ ተከላከሉ የሚል ትርጉም የለሽ ብይን ሰጥቷል። በህወሀት ታጋዮች የተሞላዉ ፍርደ ገምድሉ የወያኔ ፍርድ ቤት እንኳን ተከሳሾቹ በተከሰሱበት ሽብር የመፈጸም ወንጀል ምንም አይነት ማስረጃ አልተገኘባቸዉም ሲል አገዛዙ ግን የፖለቲካ ክንዱን በመጠቀም ማስረጃ ያልተገኘባቸዉን ሠላማዊ ዜጎች የተከሰሱበትን መሰረተ ቢስ ክስ ተከላከሉ የሚል የፖለቲካ ዉሳኔ ሰጥቷል።
የወያኔ አገዛዝ የሙስሊሙን ህብረተሰብ የመፍትሄ አፈላላጊ ቡድን መሪዎች ፍርድ ቤት ያቀረባቸዉ ለምዕራባዉያን ለጋሾቹና ለአለም አቀፍ አበዳሪ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍትህ ያለ ለማስመሰል ነዉ እንጂ ወያኔ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን የፈረደባቸዉ ያሰራቸዉ ቀን ነዉ። የወያኔ የፍትህ ታሪክ በግልጽ እንደሚያሳየን ወያኔ ግለሰቦችን የሚያስረዉ ለክስ የሚያበቃ ማስረጃ አግኝቶባቸዉ አይደለም፤ ይልቁንም ወያኔ ማስረጃዎችን እየፈበረከ ለፍረድ ቤቶች የሚያቀርበዉ ግለሰቦችን ካሰረና ሰብዓዊ መብታቸዉን ከገፈፈ በኋላ ነዉ። ለምሳሌ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን አስሮ ብዙም ሳይቆይ የእነዚህን ሰላማዊ ዜጎች ተክለ ሰዉነት ጥላሸት የቀባና ግለሰቦቹን ያለ ማስረጃ ወንጀለኛ አድርጎ የፈረጀዉን “ጂሐዳዊ ሀረካት” የሚል የፈጠራ ድራማ ሰርቶ ለህዝብ አቅርቧል።
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሽብር በመፈጸም ወንጀል ተጠርጥረዉ የቀረቡለትን ግለሰቦች በተከሰሱበት ወንጀል ማስረጃ አላገኘሁባቸዉም ካለ በኋላ ሁሉንም በነጻ አለማሰናበቱ የሚያሳየን የወያኔ ፍርድ ቤቶች ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነጻ አለመሆናቸዉን ብቻ ሳይሆን፤ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍርድ ቤቶች የገዢዉ ፓርቲ የማጥቂያ መሳሪያዎች መሆናቸዉን ጭምር ነዉ። የወያኔን አገዛዝ ከሌሎች አምባገነኖች ለይቶ አደገኛ የሚያደርገዉና በምዕራባዉያን መንግስታትና በቀላጤዎቻቸዉ እንዲወደስ ያደረገዉም ይሄዉ አገዛዙ የሚቃወሙትን ኃይሎች የሚያጠፋቸዉ እንደሌሎቹ አምባገነኖች በግልጽ ሳይሆን በህግ ሽፋን ዉስጥ በስዉር መሆኑ ነዉ።
የወያኔዉ ፍርድ ቤት በተመሳሳይ ወንጀል ተከስሰዉ የቀረቡለትን ነገር ግን ምንም መረጃ ያላገኘባቸዉን የድምጻችን ይሰማ መሪዎች ገሚሶቹን በነፃ ለቅቆ የተቀሩትን ጥፋተኛ አለመሆናችሁን አረጋግጡ ብሎ መወሰኑ የወያኔን ሁለት እኩይ አላማዎች ያሳየናል። የመጀመሪያዉ የወያኔ አላማ በአላማቸዉ ጸንተዉ የቆሙትን የድምጻችን ይሰማ መሪዎች መከፋፈል ሲሆን፤ ሁለተኛ አላማዉ ደግሞ የኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች የቀረቡላቸዉን የክስ መዝገቦች በሚገባ አጣርተዉ ዉሳኔ የሚሰጡ መሆናቸዉን ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ ለማሳየት ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ግን እንደዚህ አይነቶቹን የወያኔ እኩይ ተግባሮች ካወቀ ዉሎ አድሯል፤ ስለሆነም ከወያኔ ፍትህ ጠብቆ አያዉቅም፤ ወያኔ የክፋትና የበቀል ምንጭ ነዉና ለደፊትም አይጠብቅም። የድምጻችን ይሰማ መሪዎችም ሆኑ ከእነሱ በፊት በግፍ ታስረዉ መከራቸዉን የሚያዩት የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፤ ጋዜጠኞችና የሲቪክ ማህበራት መሪዎች የታሰሩት ለቆሙለት የፍትህ፤ የነጻነትና የእኩልነት አላማ እንደ አለት ጸንተዉ በመቆማቸዉ ነዉ። እነዚህ ጀግኖች የታሰሩለት አላማ የሁላችንም አላማ ነዉና ፍትህ፤ እኩልነትና ነጻነት የጠማን ኢትዮጵያዉያን ክንዳችንን አስተባብረን የችግሮቻችን ሁሉ ምንጭ በሆነዉ በወያኔ ስርዐት ላይ ክንዳችንን በጋራ እናንሳ!

Thursday, December 19, 2013

ኦባንግ ከደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ጋር ተነጋገሩ “በራችሁን ዘግታችሁ እርቅ አውርዱ”


“ባለውለታችሁ የኢትዮጵያ ህዝብ አዝኖባችኋል፣ አርቃችሁ እዩ”
“በትግሉ ወቅት ለነጻነት ስትዋደቁ ኢትዮጵያ በጋምቤላ አኙዋክ ምድር ላይ ሙሉ ከለላና ዋስትና በመስጠት ያበረከተችው አስተዋጽኦ የሚረሳ ነው? ከነጻነት ታጋዮችችሁ ጎን በመሰለፍ ብረት ያነሱ የአኙዋክ ኢትዮጵያውያን ልጆች መስዋዕትነት ይዘነጋችኋል? አሁን ድረስ የትግሉ የመስዋዕትነት ቁስላቸው ያልዳነ የአኙዋክ ልጆች እንዳሉ ትዘነጋላችሁ?” በማለት የተናገሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ /ጥቁሩ ሰው/ ናቸው።Obang Metho and South Sudan
በታላላቅ መድረኮችና በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ተሰሚነታቸውና ስብዕናቸው እየጎላ የሄደው ጥቁሩ ሰው ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ ከላይ የተገለጸውን ህሊና የሚፈታተን ጥያቄ ያቀረቡት ለደቡብ ሱዳን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ባርናባ ማሪያል ቤንጃሚን ነው። ለረዥም ሰዓት ጊዜ ወስደው ውይይት ማድረጋቸውን ተከትሎ የጎልጉል የአሜሪካ ዘጋቢ እንደዘገበው አቶ ኦባንግ ዶ/ር ባርናባን ያገኟቸው አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ነበር።
በጁባ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መደረጉ ይፋ ከተደረገበት አንድ ቀን በፊት አስቀድሞ በተያዘ የውይይት መርሃ ግብር የተገናኙት ዶ/ር ባርናባና አቶ ኦባንግ በርካታ ወቅታዊ ጉዳዮችን አንስተው መነጋገራቸው ታውቋል። አቶ ኦባንግ የደቡብ ሱዳን የነጻነት ትግል ወቅት ኢትዮጵያ በመንግስት ደረጃ የሰጠችውን ሙሉ ድጋፍና፣ ድንበር ሳይከልላቸው በሁለቱም አገራት የሚገኙት የአኙዋክ ልጆች ትግሉን የነፍስ ዋጋ በመክፈል መደገፋቸውን በማስታወስ በውይይቱ ወቅት ያነሱት ያለ ምክንያት አልነበረም።
“በጆን ጋራንግ ይመራ የነበረው ትግል ፍሬ አፍርቶ ደቡብ ሱዳን ነጻ ስትወጣ የማይረሳ ውለታ ለሰራቸው ኢትዮጵያና የአኙዋክ ልጆች የተከፈላቸው ብድር አሳዛኝና የወደፊቱን ጊዜ ያላገናዘበ ነው” በማለት በውይይቱ ስለተነሱ ነጥቦች ማብራሪያ የሰጡት አቶ ኦባንግ፣ “ለህዝቦች ነጻነትና ለሰብአዊ መብት መከበር የታገለ ድርጅትና አመራሮች ለነጻነታቸው የተከፈለላቸውን የደም ዕዳ ያወራረዱትና እያወራረዱ ያሉት ከወያኔ መሪዎች ጋር በማበር ከለላ የጠየቁ ህጋዊ ስደተኞችን እያፈኑ ለወያኔ አሳልፎ በመስጠት መሆኑ አሳዝኖኛል። ኢትዮጵያዊያን አዝነዋል” በማለት ነበር።
ህጋዊ ከለላ የጠየቁ ስደተኞች ቶርቸር እንዲደረጉ፣ እንዲገደሉ፣ እንዲታሰሩና ኢሰብአዊ ግፍ እንዲፈጸምባቸው ለአምባገነኖች አሳልፎ መስጠት ዘግይቶም ቢሆን ዋጋ እንደሚያስከፍል አቶ ኦባንግ አስረግጠው ተናግረዋል። በ1993 የአኙዋክ ጄኖሳይድ /የጅምላ ጭፍጨፋ/ ሸሽተው በስደት ደቡብ ሱዳን የገቡ የአኙዋክ ልጆችን ለገዳዩ የወያኔ አንጋች ሃይል ማስረከብ መቆም እንዳለበት ያሳሰቡት አቶ ኦባንግ “ይህንን ተግባር የፈጸሙትም ቢያንስ ዓለም አቀፋዊውን ህግ ተላልፈዋልና ሊጠየቁ ይገባል። እርስዎም ይህንኑ የማስፈጸም ሃላፊነት ይኖርብዎታል” በማለት ለውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
የአኙዋክና የበኩር ልጆችና የደቡብ ሱዳን ግንኙነት ከድንበር ያለፈ የደም ትስስርና ኢትዮጵያ የማይረሳ ውለታ በመክፈል ያከበረችው ውህደት በመሆኑ መንግስታቸው ቆም ብሎ ሊያስብ እንደሚገባው አቶ ኦባንግ ምክር አዘል መልዕክት ማስተላለፋቸውን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ አስተማማኝ ከለላና ዋስትና በመስጠት የፈጸመችውን ሊዘነጋ የማይችል ተግባር አለማክበር ለወደፊቱ ወዳጅ የሚያሳጣ ብድር ለራስ የማስቀመጥ ያህል እንደሆነም በወጉ እንዲገነዘቡ ሚኒስትሩን ተማጽነዋል።
አምባገነኑና በህዝብ የሚጠላው የህወሃት አገዛዝ እድሜ አሁን ካለው ትውልድ እድሜ በላይ ዘሎ የሚሄድ ባለመሆኑ በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን ማቅረብ፣ መተዋወቅና መልካም ግንኙነት መመስረት ለወደፊቱ ጠቃሚ መሆኑንም አስረድተዋል። እርሳቸው በዋና ዳይሬክተርነት የሚመሩት ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄም /አኢጋን/ ከተመሰረተበት ዓላማ አንጻር የደቡብ ሱዳን መንግሥት ህወሃት/ኢህአዴግን ለማስደሰት ሲል ኢትዮጵያዊያን ላይ ፈጸመውና እየፈጸመ ባለው ተግባር ያዘኑ ወገኖች የቀድሞውን የፍቅር መንገድ እንዲከተሉ አበክሮ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ሕዝብ ያልወደደው መንግስትና ህዝብ ያልተቀበለው ኢንቨስትመንት መጨረሻው ኪሳራ በመሆኑ የደቡብ ሱዳን መንግስት ሊጠነቀቅ እንደሚገባው አቶ ኦባንግ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ነግረዋቸዋል። ከደቡብ ሱዳን ተነስቶ በጋምቤላ አድርጎ ወደ ኬኒያና ጅቡቲ ይዘረጋል የተባለው የነዳጅ ማስተላለፊያ ቱቦ ሕዝብን በመግፋትና በመበደል ከቶውንም ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችል ያለማቅማማት ጠቁመዋል።
ህዋሀት በጋምቤላ ንጹሃንን ከቀያቸው በጠመንጃ ሃይል በማባረር፣ መሬታቸውን በሳንቲም ቸብችቦ፣ የህይወታቸው ዋስትና የሆነውን ደናቸውን አስጨፍጭፎ፣ ለምን በማለት የጠየቁትን አስሮና ገድሎ ያቋቋመው ኢንቨስትመንት በዜሮ መጣፋቱን ለአብነት ጠቅሰው ማስረዳታቸው የጠቆሙት ጥቁሩ ሰው “ኢንቨስትመንት መልካም ነው። ህዝብ ካልተቀበለው ተግባራዊ ሊሆን አይችልም። ህዝብ ይሁንታ የማይሰጠው ኢንቨስትመንት ፍሬ አያፈራም። ከውስጥም ከውጪም ያላችሁን ግንኙነት መርምሩ። ያዘኑባችሁ ተበራክተዋል” ሲሉ መክረዋል።
በአዲስ የምትቋቋመው “አዲሲቷ ኢትዮጵያ” ለደቡብ ሱዳን ወንድምና እህቶች ጭምር ቦታ በማዘጋጀት መሆኑንን አቶ ኦባንግ አረጋግጠው “በሌላ በኩል ደግሞ በአሁኑ ወቅት ስጋት ውስጥ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለዲሞክራሲ መከበርና ለነጻነት በተከፈለው መስዋዕት የተገኘውን ድል የደቡብ ሱዳን መንግስት በአግባቡ እየተጠቀመበት አለመሆኑን አቶ ኦባንግ ለውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል። አዲሲቷ ደቡብ ሱዳን ከድል በኋላ የትግሉን መሐላ ሙሉ በሙሉ ረግጣለች በማለት መሪዎቹን ወቅሰዋል።
ከድል በኋላ በደቡብ ሱዳን በርካታ ችግሮች መከሰታቸውን በመዘርዘር የማስጠንቀቂያ ምክር መሰንዘራቸውን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አሁን ባለው ሁኔታ በደቡብ ሱዳን ባሉ ሃያ አንድ ጎሳዎች መካከል ቀውስ መፈጠሩ አይቀርም። ስለዚህ በራችሁን ዘግታችሁ እርቅ አውርዱ። በቀደሙት ሰማዐታቶች ደምና አጥንት ላይ ዴሞክራሲን መስርቱ። ይህንን ካላደረጋችሁና አሁን በያዛችሁት የአምባገነንነትና የአንድ ሰው ወይም ጎሣ የበላይነት መንገድ ከቀጠላችሁ ጣጣው ወደኛም ያመራል” ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን አስጠንቅቀዋቸዋል። አሁን ያለው የውስጥ ሽኩቻ መልኩን ሳይቀይር መፍጠን እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋቸዋል። (አቶ ኦባንግ ይህንን ለውጭ ጉዳይ ሚ/ሩ የተናገሩት እሁድ መፈንቅለ መንግሥት ከመሞከሩና አሁን ደግሞ በዘር /ጎሣ/ መስመር ተከፋፍለው ደቡብ ሱዳናውያን መጫረስ ከመጀመራቸው አንድ ቀን በፊት ነበር)
በደቡብ ሱዳን እውነተኛ እርቅ ለማውረድ የአኙዋክ የፍትሕ ምክርቤት አንድ ግብረ ሃይል ወደ ጁባ እንደሚልክ መረጃ እንዳላቸው የጠቆሙት አቶ ኦባንግ በውይይቱ ወቅት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቀና ምላሽ ማግኘታቸውን አመልክተዋል። በመጨረሻም አቶ ኦባንግ የሚመሩት ድርጅት ኢትዮጵያ ውስጥ የእርቅ ደጆች የሚከፈቱበት አግባብ ላይ ከሚመለከታቸው ተጽዕኖ አድጊራዎችና አቅሙ ካላቸው አካላት ጋር እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸውላቸዋል። በማያያዝም “እኛ ሩቅ እያየን እየሰራን ነው። እኛ በስፋት እያሰብን በመራመድ ላይ ነን።
በስፋት አስበን፣ ሩቅ እያየን ስንሰራ እናንተንም አንዘነጋም። በተቃራኒው እናንተ ለነጻነታችሁ የተዋደቁላችሁን የራሳችሁን ዜጎች እያነቃችሁ ለወያኔ አሳልፋችሁ ትሰጣላችሁ። ደም ያፈሰሱላችሁንና አጥንታቸውን የከሰከሱላችሁን ውድ ዜጎች ሳትታረቁ በምድራቸው ላይ ቱቦ ዘርግታችሁ ብር ልታመርቱ ታቅዳላችሁ። ይህ ከቶውንም ጤነኛ አካሄድ አይደለምና ህዝብን አስቀድሙ። አብረን እንስራ። ይህ መልካም ጅምር ነው” በማለት መሰናበታቸውን አቶ ኦባንግ ለጎልጉል ተናግረዋል።
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክትር አቶ ኦባንግ ሜቶ ከደቡብ ሱዳን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ባርናባ ማሪያል ጋር ለመወያየት የቻሉት ሚኒስትሩ አሜሪካ ከመምጣታቸው በፊት በኤምባሲያቸው አማካይነት አስቀድሞ በተያዘ መርሃ ግብር መሰረት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። በውይይቱ ወቅት ሚኒስትሩ ስለ ሰጡት አስተያየትና ምላሽ አቶ ኦባንግ በዝርዝር ለመናገር አልፈለጉም። አቶ ኦባንግ በትውልድ አኙዋክ ቢሆኑም እርሳቸው የሚመሩት ድርጅት /አኢጋን/ ኢትዮጵያውያን ከአገራቸው ውጭ በስደት በሚሰቃዩበት ቦታ ዘር፣ ቀለም፣ ጎሣ፣ ቋንቋ፣ ወዘተ ሳይለይ ፈጥኖ በመድረስ እርዳታ በማድረግ እርሳቸውም በተመሳሳይ ተግባር ተጠምደው በቅንነት በማገልገል እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የእርቅ ደጆች እንዲከፈቱ አግባብ ካላቸውና አቅሙ ካላቸው ክፍሎች ጋር እየሰራን ነው በማለት አቶ ኦባንግ ለሚኒስትሩ የገለጹላቸውን ሃሳብ እንዲያብራሩ ከጎልጉል ተጠይቀው “ሁሌም የእርቅ ደጆች እንዲከፈቱ እንሰራለን። ይህ የጋራ ንቅናቄውና አርቀው የሚመለከቱ ዜጎች ሁሉ እምነት ነው። ብዙ ስራ እየሰራን ነው። ስንጨብጠውና ለህዝብ ሪፖርት የምናቀርብበት አሳማኝ ጊዜ ላይ ስንደርስ ብቻ ይፋ እናደርጋለን። ስራው በባህሪው ከንግግር በመቆጠብ ተግባር ላይ ማተኮርን ስለሚጠይቅ እኛም ባናወራው ጊዜው ሲደርስ ሁሉም በየፊናው የሚገልጸው ይሆናል። ስራው ሳይሰራ ፕሮፓጋንዳው ከቀደመ በሁሉም ወገን ተዓማኒነትን የማጣትና የመጣል አደጋ አለው። የኢትዮጵያ ህዝብ ተግባር የናፈቀው ይመስለኛል” የሚል ድፍን መልስ ሰጥተዋል።